By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የአፄዎቹ እና አዞዎቹ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችአርባምንጭ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግፋሲል ከነማ

የጨዋታ ዘገባ | የአፄዎቹ እና አዞዎቹ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በሊጉ የ23ኛ ሳምንት ሁለተኛ መርሀግብር ፋሲል ከነማን ከአርባምንጭ ከተማ አገናኝቶ 1 – 1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል ።

ፋሲል ከነማዎች በ22ኛው ሳምንት ሀድያ ሆሳዕናን በረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው ምርጥ አስራ አንድ አራት ቅያሪዎችን በማድረግ አስቻለው ታመነ ፣ አምሳሉ ጥላሁን ፣ ዱላ ሙላቱ እና በዛብህ መለዮን በሽመክት ጉግሳ ፣ ሱራፌል ዳኛቸው ፣ ሀብታሙ ገዛኸኝ እና ዓለብርሀን ይግዛው ተክተው ወደ ሜዳ ሲገቡ በአርባምንጭ ከተማ በኩል ደግሞ ከባህር ዳር ከተማ አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ ሶስት ለውጦችን በማድረግ ይስሀቅ ተገኝ፣ አቡበከር ሻሚል እና ሱራፌል ዳንኤልን በመኮንን መርዶኪዮስ ፣ መሪሁን መስቀለ እና አህመድ ሁሴን ተክተው ገብተዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ሁለቱም ክለቦች በጥሩ ፉክክር የጀመሩት ነበር ። በተለይም የመጀመሪያ አስር ደቂቃዎች ላይ በአፄዎቹም ሆነ በአርባምንጭ ከተማ በኩል ዘደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ጥረቶችና አድርገዋል ።

- ማሰታውቂያ -

በአጋማሹ ቀዳሚ የግብ ሙከራም በ9ኛው ደቂቃ ላይ ሀብታሙ ገዛኸኝ ከመስመር ይዞ የሄደውን ኳስ ወደ ግብ ሞክሮ ግብ ጠባቂው ይስሀቅ ተገኝ ግብ ከመሆን አድኖታል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ከሙከራዎች የራቀው ጨዋታው ተመስገን ደረሰ በ26ኛው ደቂቃ ላይ ባደረገው ሙከራ ሌላ የግብ ዕድል አስመልክቶናል ። ጨዋታው በመጀመሪያ ደቂቃዎች በነበረው ልክ ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ መመላለሶች ባይታዩበትም በሁለቱም በኩል የግብ አጋጣሚዎችን ለማግኘት ከመጣር አላረፉም ።

ውጤታማ ያልሆኑ የማጥቃቱ የሶስተኛው ዞን የኳስ ፍሰቶች በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ እና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመሩት ቡድኖች ኳስ እና መረብና ከማገናኘት አግዷቸዋል ።

በመጀመሪያው አጋማሽ የመጨረሻ አስር ደቂቃዎች ላይ የተሻለ የማጥቃት ጫና ፈጥረው መጫወት የቻሉት አርባምንጭ ከተማዎች በ41ኛው ደቂቃ ላይ ልፋታቸው ፍሬ አፍርቷል ።

በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ ከመስመር የተነሳው ኳስ በኤሪክ ካፓይቶ በኩል ለተመስገን ደረሰ ደርሶ ተመስገን አዞዎቹን መሪ ያደረገ ግብ በፋሲል ከነማ መረብ ላይ አሳርፏል ።

የመጀመሪያው አጋማሽም በአርባምንጭ ከተማ የ1 – 0 መሪነት ተጠናቋል ።

ከዕረፍት መልስ ወደ ጨዋታው የሚመልሳቸዉን ግብ ለማስቆጠር በመጠኑም ቢሆን ከመጀመሪያው አጋማሽ የቸሻለ መንቀሳቀስ የቻሉት አፄዎቹ በ56ተኛዉ ደቂቃ ላይ በሀብታሙ ገዛኸኝ አማካኝነት ጥሩ የሚባል የግብ ዕድል መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸዉ ቀርቷል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም ጫናቸውን የቀጠሉት ፋሲል ከነማዎች በ68ተኛዉ ደቂቃ ላይ በአማካዩ ሱራፌል ዳኛቸዉ አማካኝነት ከሳጥን ውጭ ጥሩ የሚባል ሙከራን ማድረግ ችለዉ የነበረ ቢሆንም በዕለቱ ድንቅ ሲንቀሳቀስ ያመሸዉ ግብ ጠባቂዉ ይስሀቅ ኳሷን እንደምን ወደ ዉጭ አውጥቷታል።

በተቃራኒው አዞዎቹ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ በመጀመሪያው አጋማሽ ካስቆጠሩ በኋላ በአብዛኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ወደ ራሳቸዉ የግብ ክልል አፈግፍገው በመከላከል አልፎ አልፎ በሚገኙ አጋጣሚዎች ተጨማሪ ግብ ለማስቆጠር ሲጥሩ የተስተዋለ ቢሆንም በ78ተኛዉ ደቂቃ ግብ አስተናግደዋል።

በዚህም አማካዩ ሱራፌል ዳኛቸዉ ከአፄዎቹ የቀኝ ማጥቃት በኩል ያሻማውን ኳስ ግብ ጠባቂዉ ይስሀቅ መቆጣጠር ባለመቻሉ ምክንያት በዛብህ መለዮ ወደ ግብነት በመቀየር ቡድኑን አቻ ማድረግ ችሏል። አፄዎቹ የአቻነት ግብ ካስቆጠሩ በኋላ በይበልጥ የመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ የማጥቃት ሀይላቸዉን አጠንክረው የቀጠሉ ቢሆንም ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ጨዋታው አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ተገባዷል።

ዉጤቱን ተከትሎ ፋሲል ከነማ በ34 ነጥቦች በነበረበት 4ተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ በተቃራኒው አርባምንጭ ከተማ ደግሞ በ24 ነጥቦች 13ተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል ።

በ24ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ግንቦት 7(ሰኞ) ከቀኑ 9:00 ጀምሮ አርባምንጭ ከተማ ከወላይታ ድቻ ሲጫወት በተከታዩ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን ይገጥማል ።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የጦና ንቦቹ እና አዳማ ከተማ ያደረጉት የዕለቱ የመጀመሪያ መርሐግብር በአቻ ዉጤት ተገባዷል !!
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የዝውውር ዜናዎችዜናዎችሸገር ከተማ

ሸገር ከተማ ተጨማሪ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ተስማማ !

fitsum Wadu By fitsum Wadu 7 months ago
የጨዋታ ዘገባ | የጦና ንቦቹ የውድድር ዓመቱ 10ኛ ድላቸውን አስመዝግበዋል
ወላይታ ድቻ የህክምና ወጪዬ አልሸፈነልኝም በሚለው ተጨዋቹ ተከሷል
የኢትዮጵያ ከ 20 ዓመት በታች ቡድን አሰላለፍ !
“እኛና መቐለዎች የምናካሂደው ጨዋታ እግር ኳስ የሰላም መሆኑን የምናረጋግጥበት ነው ሊሆን የሚገባው”አምሳሉ ጥላሁን /ፋሲል ከነማ/
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?