መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ለክለብ ህክምና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ለክለብ ህክምና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ከአጋሮቹ ጋር በመሆን እንዲሁም በተናጥል ለስፖርቱ ባለሙያዎች የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ሲሰጥ መቆየቱ ይታወቃል። ባለፉት ወቅቶች ለአሰልጣኞች፣ ዳኞች፣ የክለብ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎችም ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱም ይታወሳል።

በተመሳሳይም በዛሬዉ ዕለት መስከረም 28 በባህር ዳር ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ በአሜሪካ የልብ ማህበር በኢትዮጵያ አማካኝነት ለህክምና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል። ለአስራ ስድስቱ የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች የህክምና ባለሙያ እና ወጌሻዎች ለአንድ ቀን በተሰጠው ስልጠና ባለሙያዎቹ ለውድድር በሚገኙበት ከተማ በእግር ኳስ ጨዋታዎች ላይ የሚከሰቱ የልብና ተያያዥ ድንገተኛ አደጋዎችን መለየትና ማከም ላይ ያተኮረ የስራ ላይ ስልጠና ነው።

በአጠቃላይም መርሃ ግብሩ በሙያው እውቀትና ልምዱ ባላቸው ባለሙያዎች በንድፈ ሃሳብና በተግባር ልምምድ ሲደገፍ ከአሜሪካ የልብ ማህበር በኢትዮጵያ የስልጠና ማዕከል ዶ/ር ሃወኒስ አሰፋ እና አቶ ብሩክ ድባቡ አሰልጥነዋል። በስተመጨረሻም ሰልጣኞች የተግባር ፈተና የተፈተኑ ሲሆን የስልጠና ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት(ላይሰንስ) ከሚመለከተው ማሰልጠኛ ማዕከል በሁለት ቀን ውስጥ እንደሚላክ ተመላክቷል።

©Escl

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...