የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ታህሳስ 28 2016 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ በ10ኛው ሳምንት በተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርቶች ከመረመረ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በሳምንቱ ከተደረጉ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና ሀዋሳ ከተማን በረታበት ጨዋታ ላይ የኢትዮጵያ ቡናው ወልደአማኑኤል ጌቱ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ሲሆን ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገድና በተጨማሪም 3 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል ተወስኗል።
እንዲሁም ስድስት ተጫዋቾች ላይ የዲሲፕሊን ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን ማይክል ኔልሰን(ሻሸመኔ ከተማ)፣ ፍሬዘር ካሳ(ባህርዳር ከተማ)፣ እዮብ ዓለማየሁ(ሃዋሳ ከተማ)፣ ሳምሶን ጥላሁን(ወልቂጤ ከተማ) እና መድሃኔ ብርሀኔ(ሃዋሳ ከተማ) ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያሰጥ ጥፋት በመፈፀማቸው ቀይ ካርድ አይተው ከጨዋታ ሜዳ በመወገዳችው ለፈፀሙት ጥፋት 1 ጨዋታ እንዲታገዱ ተወስኖባቸዋል ።
- ማሰታውቂያ -
በክለቦች ደረጃ በተላለፈ ውሳኔ ከቅዱስ ጊዮርጊስ አምስት ተጫዋቾች ፤ ከሃዋሳ ከተማ አምስት ተጫዋቾች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቡና ስድስት ተጭዋቾች በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ክለቦቹ የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍሉ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል ።
በተጨማሪም የሀምበሪቾ ዱራሜ ቡድን መሪ በቅድመ ጨዋታ ስብሰባ ባለመገኘቱ በፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ መሰረት 5 ሺህ ብር እንዲከፍል ተወስኗል።