መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የኢት.ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ዙር የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች ዳኞች ታውቀዋል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የኢት.ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ዙር የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች ዳኞች ታውቀዋል

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ ለ15ኛ ሳምንት የሊጉ መርሃግብር በዳኝነት የተመደቡትን 16 ዳኞች ይፋ አድርጓል።

በዚህ መሰረት በመሃል ዳኝነት የተመረጡት 10 ዳኞች ኢንተ.አርቢትር ሊዲያ ታፈሰ፣ ኢንተ.አርቢትር በላይ ታደሰ፣ ኢንተ.አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ፣ ኢንተ.አሸብር ሰቦቃ ፣ ፌዴራል አርቢትር ኢያሱ ፈንቴ፣ ፌዴራል አርቢትር አዳነ ወርቁ፣ ፌዴራል አርቢትር ዳንኤል ይታገሱ፣ ፌዴራል አርቢትር ሰለሞን አሸብርና ና መሆናቸው ታውቋል።

በረዳት ዳኝነት የተመረጡት ሁለቱ ወንድማማቾች ፌዴራል ረዳት ዳኞች መሃመድ ሁሴንና ሚፍታህ ሁሴንን ጨምሮ ደግሞ ፌዴ. ረዳት አርቢትር ዳንኤል ጥበቡ፣ ፌዴ. ረዳት አርቢትር አስቻለሁ ወርቁ፣ ፌዴ. ረዳት አርቢትር ሶርሳ ዱጉማ፣ ፌዴራል .ረዳት አርቢትር ማህደር ማረኝ፣ ፌዴራል ረዳት አርቢትር እሱባለሁ መብራቱና ፌዴ. ረዳት አርቢትር ታምሩ አደም መሆናቸው ታውቋል።

16ቱ አርቢትሮች ዛሬ ተጠቃለው ድሬዳዋ የገቡ ሲሆን አወዳዳሪ አካሉ ከዳኞች ኮሚቴ ከተወከለው ባለሙያ ጋር በመሆን ከ16ቱ ዳኞች ጨዋታዎችን የሚመሩትን አርቢትሮች ይመድባሉ ተብሎም ይጠበቃል

ሊግ ኩባንያው ባወጣው መርሃግብር መሠረት ውድድሩ ነገ የሚቀጥል ሲሆን ከቀኑ 10 እና ከምሽቱ 1 ሰዓት ጨዋታዎቹ በድሬዳዋ የሚካሄዱ መሆናቸው ታውቋል። ሃሙስ አርባምንጭ ከተማ ከሀዋሳ ከተማ አዳማ ከተማ ከወልቂጤ ከተማ ዓርብ ሀድያ ሆሳዕና ከኢትዮጵያ መድን ለገጣፎ ለገዳዲ ከመቻል ቅዳሜ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡና ከፋሲል ከተማ እሁድ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከድሬዳዋ ከተማ ባህርዳር ከተማ ከወላይታ ድቻ ይጫወታሉ።

ፕሪሚየር ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ29 ነጥብና 22 ግብ ሲመራ ኢትዮጵያ መድንና ባህር ዳር ከተማ በ27 እና 26 ነጥቦች ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። የፈረሰኞቹ እስማኤል ኦሮ አጎሮ በ14 ግብ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን እየመራ ይገኛል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...