የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ሰኔ 10 2016 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በሳምንቱ መርሃ ግብር በተደረጉ ጨዋታዎች ሰባት በመሸናነፍ ቀሪ አንዱ በአቻ ውጤት ሲጠናቀቅ 22 ጎሎች በ20 ተጫዋቾች ተቆጥረዋል። 18 ቢጫ ካርድ ለተጫዋቾችና ቡድን አመራሮች ሲሰጥ የተመዘገበ ቀይ ካርድ የለም።
በሳምንቱ በአንድ ተጫዋች ላይ የዲሲፕሊን ውሳኔ ተላልፏል። ጸጋዬ አበራ(ባህር ዳር ከተማ) ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ27 ኛ ሳምንት ጨዋታ ጎል ካስቆጠረ በኋላ የማዕዘን ባንዲራ ስለመስበሩ ሪፖርት ተደርጎበታል። በመሆኑም ተጫዋቹ ባጠፋው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ብር 10, 000 /አስር ሺ/ እንዲከፍል በተጨማሪም የተሰበረውን ንብረት እንዲተካ ወይም እወዳዳሪው በሚያቀርበው ማስረጃ መሰረት የንብረቱን ዋጋ እንዲከፍል ተወስኗል፡፡