By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.

መብራት ሀይል

መብራት ሀይል

ሙሉ ስም ፡ የኢትዮጵያ መብራት ሀይል ስፖርት ክለብ                        eletric

የምስረታ ጊዜ ፡ 1953 ዓ/ም

የወቅቱ አሰልጣኝ ፡ ብርሃኑ ባዬ

ም/አሰልጣኝ ፡ ኤርሚያስ ታፈረ

የበረኛ አሰልጣኝ :- ቅጣው ሙሉ

አምበል ፡ አዲሱ ነጋሽ
የህክምና ባለሙያ ፡– ጌታቸው ኃ/መስቀል

ክብሮች: – የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን – 1985, 1990, 1993

መብራት ሀይል ተብሎ በአጭሩ የሚጠራው የእግር ኳስ ክለብ በ 1953 ዓ/ም የተመሰረተና በቀጣዩ አመት 2003 ዓ/ም 50ኛ አመቱን የሚያከብር አንጋፋ ክለብ ነው፡፡ ክለቡ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤታማ ሆኖ ቢቆይም በቅርብ አመታት ግል ከሊጉ ላለመውረድ የሚታገል ክለብ ሆኗል፡፡

ምስረታ 

የአሁኑ የኢትዮጵያ መብራት ሀይል ስፖርት ክለብ የተመሰረተው በ 1953 የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ክለብ በሚል በ 1953 ዓ/ም ነው ለክለቡ በጀት የሚመድብለትና በባለቤትነት የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ መብራት ሀይል ባለስልጣን ነው፡፡ ክለቡ በርካታ ወጣት ተጫዋቾችን በመመልመልና ለትልቅ ውጤታ ለማብቃት ይታወቃል፡፡ ኤልያስ ጁሀር፣ ዮርዳኖስ አባይ፣ ታፈሰ ተስፋዬ ከዚህ ክለብ የተገኙ መሆናቸው ለዚህ ማሳያ ይሆናል፡፡

ክለቡ ከተመሰረተ ረዥም ጊዜ ቢያስቆጥርም ለመጀመሪያ ዋንጫ ለማግኘት የበቃው በ 1985 ዓ/ም ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሻምፒዮን በመሆን ታሪካዊ ድል አስመዘገበ፡፡ የወቅቱ የቡድኑ አሰልጣኝ የነበሩት ወንድማገኝ ከበደ ናቸው በዚህ አመት የጥሎ ማለፉንም ዋንጫ በመውሰድ የጣምራ ድል Double winner ባለቤት ሆኖ ነበር፡፡

አይረሴ ዘመናት 1990 እና 1993 

መብራት ሀይል የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ተብሎ ይጠራ የነበረው ውድድር ወደ ሊግ ፎርማት ተቀይሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚል ስያሜ አግኝቶ መካሔድ ሲጀምር የመጀመረያውን ዋንጫ በማንሳት ቀዳሚ ክለብ ነው፡፡ በሳምንቱ ክለቦች መካከል የተደረገውን ውድድር ለማጠናቀቅ ሻምፒዮን ሆነ፡፡ የጥሎ ማለፉንም ዋንጫ ደርቦ በመውሰድ የድርብ ድል ባለቤት ከሦስት አመት በኃላ በድጋሚ ሆነ፡፡ ይህን ዋንጫ በማንሳት ውጤታማ ሆኗል፡፡ በ 1993 የተካሔደውን ውድድር በሙሉ የበላይነት ሲያጠናቅቅ በሁለተኛው ዙር ያደረጋቸውን ጨዋታዎች ባጠቃላይ በማሸነፍ መሆኑ የወቅቱ የቡድኑን ስብስብ ጥንካሬ ያሳያል፡፡ አንዋር ያሲን፣ አንዋር ሲራጅ፣ ኤልያስ ጁሀር እና ወንድማማቾቹ ስምኦን አባይና ዮርዳኖስ አባይ የዚህ ቡድን አባለት ከነበሩት ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ አመት 1993 ለመብራት ሀይል ልዩ አመት ነበር ማለት ይችላል፡፡ ከፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ በተጨማሪ የሦስትዮሽ ድል ባለቤት የሆኑበት ዓመት ነበር፡፡

ላለመውረድ የሚታገለው መብራት ሀይል 

የመብራት ሀይል እግር ኳስ ክለብ ውጤታማ ተብለው ከሚጠቀሱ የሀገሪቱ ክለቦች አንዱ ቢሆንም በቅርብ አመታት ግን ውጤት ርቆት ወደ ብሔራዊ ሊግ ላለመውረድ በመታገል ላይ ነው በተለይም በ 2001 እና 2002 የውድድር ዘመን በሊጉ የደረጃ ሠንጠረዥ መጨረሻ አካባቢ በመሆን የመውረድ ስጋት አንዣቦበታል፡፡ የክለቡ ስብስብ ላለመውረድ ከሚፎካከራቸው ክለቦች ይልቅ የተሻለ ነው ቢባልም ውጤት ርቆታል፡፡ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ ከመጀመሪያው እስካሁን በመዝለቅ ከሚታወቁ ጥቂት ክለቦች አንዱ የሆነው መብራት ሀይል ወደ ብሔራዊ ሊግ ከወረደ በታሪክ የመጀመሪያው ይሆናል፡፡

መብራት በኢንተርናሽናል ውድድሮች 

መብራት ሀይል ሦስት ጊዜ የኢትዮጵያ ሻምፒዮን መሆን የቻለ ክለብ በመሆኑ ሦስት ጊዜ በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ የመሳተፍ እድል አግኝቷል፡፡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ዋንጫን ካነሳ በኃላ በ1986 የአፍሪካ ሻምፒዮን ክለቦች ሻምፒዮና ተብሎ ይጠራ በነበረበት ወቅት ነው የተሳተፈው፡፡ በዚህ ውድድር በቅድመ ማጣሪያው የሩዋንዳ ኢዩሹ ስፖርትን 5ለ4 በሆነ ድምር ውጤት አሸንፎ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችሎ ነበር፡፡ ይሁንና በአንደኛው ዙር ከኬንያው ጎርማሃያ ጋር ሦስት አቻ ተለያይቶ ከሜዳ ውጭ ባገባ በሚለው ሕግ ተበልጦ ወደ ሁለተኛው ዙር ሳያልፍ ቀርቷል፡፡  የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማንሳቱን ተከትሎ በ 1991 ዳግም በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲሳተፍ በኡጋንዳው ቪላ ኪጋሊ 7 ለ 2 በሆነ ሰፊ ውጤት ተሸንፎ ወጥቷል፡፡ ኪጋሊ ላይ 5 ለ 0 መሸነፉ ነበር የመልሱን ጨዋታ ያከበደበት በ 1999 ለሦስተኛ ጊዜ እድሉን ሲያገኝ በኬንያው አሰርያን ፈስታክ 3 ለ 1 ተሸንፎ ከቅድመ ማጣሪያው ደረጃ ሳያልፍ ቀርቷል፡፡

ሌላው መብራት ሀይል የተሳተፈበት ካፍ ካፕ ተብሎ ይጠራ የነበረውና አሁን የተቋረጠው ውድድር ነው በ 1988 በሞዛምቢኩ ፎሮቪያርዮ 2 ለ 0 ተሸንፎ በአንደኛ ዙር ቀረ፡፡ በ 1990 የታንዛኒያው ምላንደግ ራሱን በማግለሉ ወደ ሁለተኛው ዙር ቢያልፍም በዛምቢያው ንቻንጋ ሬንጀርስ 2 ለ 1 ተሸንፎ ተሰናበተ፡፡ በ 1993 የታንዛኒያውን ምትብዋ ሹጋርን አሸንፎ ካለፈ በኃላ በሁለተኛው ዙር በአልጄርያው ጄ ኤስ ካቢልዬ ተበልጦ ወደ ሩብ ፍፃሜው ሳይልፍ ቀርቷል፡፡

about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?