” የአትሌቲክስ ውድድሩ ዓላማ ሀገር የሚጠቅሙ
አትሌቶችን ማፍራትም ጭምር ነው”
አትሌት ተሰማ አብሽሮ
/የኬሮድ የአትሌቲክስና የልማት ማህበር ፕሬዝዳንት/
“የአትሌቲክስ ውድድሩ ያለምንም ችግር
እንደሚካሄድ እምነቱ አለን”
አቶ አወል ጅማቶ
/የጉራጌ ዞን የወጣ/ስፖርት ቢሮ ሃላፊ/
የወልቂጤ ህዝብ እንግዳ ተቀባይና ሀገሩን የሚወድ ሰላማዊ በመሆኑ በከተማዋ የሚካሄደው ውድድር ያለ አንዳች ችግር እንደሚከናወን ርግጠኛ መሆናቸውን አንድ የዞኑ የስራ ሃላፊ ተናገሩ።
- ማሰታውቂያ -
ሶስተኛው ኬሮድ ሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ የ15 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር የፊታችን ሀምሌ በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ ስለመካሄዱ ብሄራዊ በሚገኘው የንብ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ላይ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ አወል ጅማቶ እንደተናገሩት “ለሰላም እንሮጣለን በሚል የሚካሄደውን የሩጫ ውድድር ህዝቡ በጉጉት እየጠበቀው ነው ነገር ግን አንዳንድ
ሚዲያዎች ህብረተሰቡን የማይገልጹ ተገቢ ያልሆኑ መረጃዎን እያስተላለፉ ነው ህብረተሰቡ ግን የመላው ኢትዮጵያ አንድነትን በሚያሳይ መልኩ ውድድሩን እንደሚያካሂድ እናምናለን እንደ ከተማም እንደ ዞንም ሰላማዊና የህዝቦችን እሴት የሚያጠናክር ውድድር እንደሚሆን እናምናለን ከጸጥታውም አንጸር ኮሚቴ ተዋቅሮ በጥሩ ሁ ኔታ እየተዘጋጀ ነው” ሲሉ ሃላፊው አስረድተዋል።
ሶስተኛው ኬሮድ ሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ የ15 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር የፊታችን ሀምሌ 9/2015 በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ “ለሰላማችን እንሩጥ” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ ከመላው ኢትዮዽያ የተውጣጡ ከ1000 በላይ አትሌቶች ይካፈላሉ ተብሎ ይጠበቃል። በውድድሩ ከ1-6ኛ ደረጃ ይዘው ላጠናቀቁ አትሌቶች የገንዘብ ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን አንደኛ ለወጡ 75 ሺህ ብር ለሁለተኛ 50 ሺህ ብር ሶስተኛ ለወጣ 25 ሺህ ብር ከ4-6ኛ ለወጡ አትሌቶች 15ሺህ 10 ሺህ እና 5 ሺህ ብር ለሽልማት መልክ መዘጋጀቱ ታውቋል።
ሀምሌ 9 ከዋናው ውድድር በፊት ለመጀመሪያ ገዜ የዊልቼር ውድድር እንደሚካሄድና በቀጣዩ አመት ለአራተኛ ጊዜ ሲካሄድ የህጻናት ውድድር እንደሚኖር የገለፁት የኬሮድ የአትሌቲክስና የልማት ማህበር ፕሬዝዳንት አትሌት ተሰማ አብሽሮ ” የሩጫው አላማ እንደ ሀገር ለአትሌቶች የውድድር እድል ፈጥሮ ሀገር የሚጠቅሙ አትሌቶች ማፍራት የህዝቡን ባህልና እሴት ማሳየት ነው ” ሲል ተናግሯል።
” ከውድድሩ አንድ ቀን አስቀድመን ሀምሌ 8/2015 ከተወዳዳሪ አትሌቶች ጋር በከተማዋ የችግኝ ተከላ እናደርጋታለን” ያለው አትሌት ተሰማ አብሽሮ ” ከ1000 በላይ አትሌቶችን ማረፊያ አዘጋጅቶ በራሱ ወጪ ትራንስፖርት አዘጋጅቶ ከአዲስ አበባ ውድድሩ ስፍራ ድረስ በትራንስፖርት ወስዶ ከውድድሩ በኋላም ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ትልቅ ድጋፍ ያደረገውን የወልቂጤ ዩኒቨርስቲን እናመሰግናለን ንብ ባንክ ግሎባል ስፖርት ኮሚኒኬሽን እና ሌሎች አጋዦችንም ከልብ አመሰግናለሁ” ሲል ተናግሯል።
በእለቱ የተገኙት የንብ ባንክ ም/ል ፕሬዝዳንት አቶ አብርሃም ” ባንካችን በመላው አገሪቱ 450 ቅርንጫፎች ከፍቶ እየሰራ ይገኛል ከዚህ የባንክ አገልግሎት ጎን ለጎን ማህበራዊ ሀላፊነታችንን እየተወጣን እንገኛለን ከነዚህም መሃል አንዱ ከኬሮድ ጋር የምንሰራው ነው በቀጣይም ሌሎች ውድድሮች ላይ አጋር እንደምንሆን አረጋግጣለሁ” በማለት ተናግረዋል።
ብሄራዊ በሚገኘው የንብ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ላይ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የለንደን ማራቶን አሸናፊዋ አትሌት የዓለም ዘርፍ የኋላ
የቶኪዮ ኦሎምፒክ አሸናፊ አትሌት ጸሀይ ገመቹና
9 ጊዜ የአለም ማራቶን አሸናፊ በተለይ ሜጀር በተባሉት የለንደን፣ የቺካጎና ኒውዮርክ ማራቶን ድል አድራጊ አትሌት
ጸጋዬ ከበደ እንዲሁም ሌሎች አትሌቶችና እንግዶች ተገኝተዋል።
ኬሮድ የሚለው የማሀበሩ የስሙ ትርጉም ” ኬር…ኦድ” ሰላም ተናገር ማለት እንደሆነም በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።