44ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፕዮና በዛሬው ዕለት በአውስትራሊያ ባትረስተ ከተማ ተደርጓል ።
በአምሰት የውድድር ዘርፎች በ28 አትሌቶች የተወከለችው ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 2 የወርቅ 7 የብር እና 1 የነሀስ ሜዳልያ በማስመዝገብ የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች ።
በዕለቱ በቀዳሚነት በተደረገው የድብልቅ ሪሌይ የ8 ኪ.ሜ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በ23:21 የኬንያ አትሌቶችን ተከትለው በሁለተኝነት አጠናቀዋል ።
በሴቶች ከ20 ዓመት በታች የ6 ኪ.ሜ ውድድር ሰናይት ጌታቸው በ20:53 በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ መዲና ኢሳ በሰባት ሰከንዶች ዘግይታ የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች ።
- ማሰታውቂያ -
ለምለም ንብረት 5ኛ ፤ መሰረት የሻነህ 7ኛ ፤ ትነበብ አስረስ 8ኛ እንዲሁም መልክናት ውዱ 11ኛ ደረጃን በመያዝ ሲያጠናቅቁ በአጠቃላይ ድምር ውጤት በ15 ነጥቦች ኢትዮጵያ የቡድን አሸናፊ ሆናለች ።በወንዶች ከ20 ዓመት በታች የ8 ኪ.ሜ ውድድር ቦኪ ድሪባ በ24:31 የሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል ። በውድድሩ ኬንያውያኑ እስማኤል ኪፕሪኩይ እና ሬይኖልድ ቼሩዮት የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል ።
በረከት ዘለቀ 5ኛ አቤል በቀለ 7ኛ በረከት ነጋ 8ኛ ኩማ ግርማ 13ኛ እንዲሀም ይስማው ድሉ በ15ኝነት ውድድራቸውን ፈፅመዋል ።
በአዋቂ ሴቶች የ10 ኪ.ሜ ውድድር ኢትዮጵያ በፅጌ ገብረሰላማ አማካኝነት የብር ሜዳልያ አስመዝግባለች ። ፅጌ የገባችበት ሰዓት 33:56 ሲሆን ውድድሩን በቀዳሚነት ካጠናቀቀችው ኬንያዊቷ ቤትሪስ ቺቤቶ በስምንት ሰከንድ ዘግይታ ነው ።
በመድረኩ ተጠብቃ የነበረችው ለተሰንበት ግደይ ውድድሩን በቀዳሚነት ለማጠናቀቅ ተቃርባ የነበረ ቢሆንም ባጋጠማት ድንገተኛ ጉዳት ውድድሩን ለማቋረጥ ተገዳለች ። ፎቲን ተስፋይ 5ኛ ፤ ሀዊ ፈይሳ 6ኛ ፤ ጌጤ አለማየሁ 12ኛ እንዲሁም ውዴ ከፋለ 15ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።
በአዋቂ ወንዶች የ10 ኪ.ሜ ውድድር በሪሁ አረጋዊ በ29:26 የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል ። በውድድሩ ኡጋንዳዊው ዳኮብ ኪፕሊሞ በ29:17 በመግባት የወርቅ ሜዳልያ ባለቤት ሆኗል ።
ሀይለማርያም አማረ 9ኛ ፤ ሞገስ ጥዑማይ 10ኛ ጪምዴሳ ደበሌ 11ኛ ሰለሞን ባረጋ 12ኛ እንዲሁም ጌታነህ ሞላ በ14ኝነት ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።