By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የፈረሰኞቹ ወጣቶች ሲቲ ካፑ ላይ ነግሰዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
መቻልቅዱስ ጊዮርጊስአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫዜናዎች

የፈረሰኞቹ ወጣቶች ሲቲ ካፑ ላይ ነግሰዋል

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 1 year ago
Share
SHARE

*… ሰባተኛ የሪከርድ ድላቸው ሆኗል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫን ለሰባተኛ ጊዜ መውሰዱን አረጋገጠ።

ፈረሰኞቹ ለ16 ጊዜ የተካሄደውን ሻምፒዮና አሸናፊ መሆናቸውን ያረጋገጡት በቀድሞ ኮከባቸው ፋሲል ተካልኝ የሚሰለጥነውን መቻልን በሀብቶም …ብቸኛ ግብ 1ለ0 መርታት በመቻላቸው ነው። ከፍጻሜ ጨዋታው አስቀድሞ በተካሄደ የደረጃ ኢትዮጵያ ቡናም ለገጣፎ ለገዳዲን 1ለ0 በማሸነፍ ሶስተኛ ሆኖ ጨርሷል።

የፈረሰኞቹ ወጣቶች በነገሱበት 16ኛው የከተማው ዋንጫ ላይ በግማሽ ፍጻሜው በመለያ የፍጹም ቅጣት ምት ኢትዮጵያ ቡናን በዋንጫው መቻልን በማሸነፍ ለነገው ክለባቸው ተስፋ መሆናቸውን ለኢትዮጵያ እግርኳስ የታዳጊዎቾ ችሎታ አለመምከኑን ያሳዩበት ሆኗል። ከዚሁ ጎን የበርካቶች ጥያቄ የሆነው ፈረሰኞቹ ከነዚህ ወጣቶች በቋሚነት እነማንን አሳድገው የወጣቶቹን ተስፋ ያለመልማሉ የሚለው ሆኗል።

- ማሰታውቂያ -

አሰልጣኝ ሳምሶን ሙሉጌታ / ፍሌክስ/ ባለልምዶቹ አሰልጣኞች ገ/መድህን ሃይሌ፣ ተመስገን ዳናና ፋሲል ተካልኝን በመብለጥ ታዳጊ መስራትና ውጤቱን ማየት ትልቅ ደስታ እንደሚፈጥር ያሳየ ህኗል። ቅዱስ ጊዮርጊስ የዘንድሮውን ጨምሮ በ2002፣ በ2003፣በ2004፣
በ2006፣በ2010፣ በ2012 የውድድሩ ሻምፒዮን በመሆናቸው የከተማውን ዋንጫ ሰባት ጊዜ በመርታት ሪከርድ መያዝ ችለዋል።

በእስካሁኑ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ቡና በ4 ድል፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ3 ድል እንዲሁም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ባህርዳር ከተማ በእኩል አንድ አንድ የዋንጫ ድል የዋንጫ አሸናፊ ክለቦች ዝርዝር ውስጥ ገብተዋል። በውድድሩ ታሪክ ከከተማው ክለቦች ውጪ ሻምፒዮን የሆነው የአምናው አሸናፊ ባህርዳር ከተማ ብቻ መሆኑ ይታወቃል። ውድድሩ በ1998 ሲጀመር ሻምፒዮን የነበረው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲሆን ሻምፒዮናው በ2000 እና በ2013 ሳይካሄድ መቅረቱም ይታወቃል። በዘንድሮ ሻምፒዮና ከዚህ ቀደም የዋንጫ ባለቤት ከሆኑ አምስት ክለቦች መሃል ሁለቱ ባህርዳር ከተማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሳይካፈሉ ቀርተዋል።

ሻምፒዮናው በስኬትና በሰላም በመጠናቀቁ መደሰታቸውን የገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ አረጋ እንደተናገሩት

“በከተማችን ፍጹም በሆነ ሰላም ሲካሄድ የነበረው ሻምፒዮና በመጠናቀቁ ተደስተናል እንደ አዘጋጅ ድግሳችንን በሰላም በማጠናቀቃችን ኩራት ተሰምቶናል በተለይ አምና በነበረው የሲቲ ካፑ ውድድር የተፈጠሩ አንዳንድ ችግሮች በክለቦች ላይ የደረሰው አላስፈላጊ ጉዳትና ውድድሩ ላይ ያጠላው መጥፎ ስሜትን የምንረሳበት ሆኖ በመጠናቀቁ ተደስተናል። በከተማችን ላይ የታየውን እግርኳሳዊ መነቃቃትን ለማስቀጠል ጠንክረን የምንሰራ ይሆናል የፌዴሬሽናችን መሪ ቃል በሆነው ‘ዕውቀታችን ለእግርኳሳችን’ ለሀገራችን በቀጣይ የተሻለ ስራ የምንሰራበት የከተማችን ወጣቶች የተሻለ እግርኳሳዊ ስኬት እንዲኖራቸው የምናግዝ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ ውድድሩ በሰላም እንዲፈጸም ትልቅ ድጋፍ ላደረጉት ለስፖርት ቤተሰቡ፣ ለክለቦች፣ ለከተማችን የጸጥታ ሃይሎችና ደፋ ቀና ሲሉ ለነበሩ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትና አጠቃላይ ሰራተኞች ውድድሩን በቀጥታ ስርጭት ሲያስተላልፍ ለነበረው አዲስ ሚዲያ ኔትወርክና ለሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ምስጋናዬን ማቅረብ እፈልጋለሁ” ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የዋሊያዎቹ አለቃ ውበቱ አባተ በተራዘመው የሁለት አመት ኮንትራታቸው 250 ሺህ ብር የተጣራ ደመወዝ እንደሚከፈላቸው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።
Next Article የዋሊያዎቹና የሱዳን የዛሬ ጨዋታ በሶማሌ ዳኞች ይመራል “ፊፋ የወዳጅነት ጨዋታን የሌላ ሀገራት ዳኞች ካልመሩት አይመዘገብም ብሎናል” የኢት.እግርኳስ ፌዴሬሽን

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
አፍሪካ ዋንጫአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች ከሜዳዉ ዉጭ እንደሚያደርግ ተረጋግጧል

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 2 years ago
አሁንም እንደ በፊቱ ቀጠሮ ላይ ቀልድ አናውቅም ከተባሉ ያለጥርጥር አባባሉ የሃትሪክ ነው…. እንዳልነው ነገ ጠዋት በቀጠሮው ሰአት እንገኛለን
ደደቢት ከ አርባምንጭ ከተማ | ኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ /LIVESCORE/ ይከታተሉ
የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ የሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በድል ጀምረዋል
አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ሲዳማ ቡናን በዋና አሰልጣኝነት ተረክቧል !
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?