ሃገር አቀፍ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር የእጣ ማወውጣት ፕሮግራም ተካሄደ!!
ወልድያ ከተማ ላይ የሚካሄደው የሃገር አቀፍ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከ ሐምሌ 22-ነሐሴ 9 ድረስ በወልድያ ከተማ በ34 የክልል ክለቦች መሃከል የሚካሄድ ሲሆን የእጣ ማውጣት ስነስርአቱ ዛሬ አርብ ሐምሌ 21 ቀን የእጣማውጣቱ ስነስርአት በወልድያ ባህል አዳራሽ ተካሂዷል!!
በዚህ ፕሮግራም መሰረት 34ቱ ክለቦች በ 8 ምድቦች ተከፍለው የሚጫወቱ ሲሆን ከየ ምድቡ ሁለት ሁለት ቡድኖች ባጠቃላይ 16 ቡድኖች ወደ ጥሎ ማለፉ ያልፋሉ!!
በጥሎማለፍ ካለፉት 16 ክለቦች ውስጥ በጥሎማለፍ ጨዋታው ወደ እሩብ ፍጻሜው የሚቀላቀሉ 8 ክለቦች ወደ ብሄራዊ ሊግ (አንደኛ ሊግ) ማለፋቸውን ያረጋግጣሉ!!
በዚህ ውድድር በውድድር ደንቡ አንቀጽ 13 ተ.ቁ 2 በአንድ ጨዋታ መቀየር የሚቻለው የተጨዋች ብዛት 3 የነበረው ወደ 4 ከፍ ብሏል ይህም በዋናነት ለወጣቶቹ እድል ለመስጠት ታስቦ ነው!!
ምድቡም
ምድብ አንድ (ሀ)
1. የጁ ፍሬ ወልድያ (አማራ)
2. ሽረ እንደስላሰ ቢ (ትግራይ)
3. ያሶ ወረዳ (ቤኒሻንጉል)
4. ሾኔ ከተማ (ደቡብ)
5. ኢተያ ከተማ (ኦሮሚያ)
.
ምድብ ሁለት (ለ)
1. ድሬዳዋ ኮተን (ድሬዳዋ)
2. ቡሬ ከተማ (አማራ)
3. መርካቶ አካባቢ (አ/አ)
4. ቤንች ማጂ ፖሊስ (ደቡብ)
5. መተከል ፖሊስ (ቤኒሻንጉል)
.
ምድብ ሶስት (ሐ)
1. አሳሳ ከተማ (ኦሮሚያ)
2. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፖሊስ
3. ደጋን ከተማ (አማራ)
4. ናኖ ሁርቡ (አ/አ)
.
ምድብ አራት (መ)
1. ነስር ክለብ (ቤኒሻንጉል)
2. ሰንዳፋ በኬ (ኦሮሚያ)
3. አረካ ከተማ (ደቡብ)
4. ዋልያ ክለብ (ድሬዳዋ)
.
ምድብ አምስት (ሠ)
1. ሀረማያ ዩንቨርስቲ (ሐረር)
2. ሻሾጎ ወረዳ (ደቡብ)
3. አላማጣ ከተማ (ትግራይ)
4. መርሳ ከተማ (አማራ)
.
ምድብ ስድስት (ረ)
1. አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ (አ/አ)
2. ሐረር ፖሊስ ኮሚሽን (ሐረር)
3. ኦሮሚያ ፖሊስ (ኦሮሚያ)
4. ገንዳ ውሃ ከተማ (አማራ)
.
ምድብ ሰባት (ሰ)
1. ገንፈል ውቅሮ (ትግራይ)
2. ጉለሌ ክ/ከተማ (አ/አ)
3. 07 ቀበሌ (ድሬዳዋ)
4. ካማሺ ከተማ (ቤኒሻንጉል)
.
ምድብ ስምንት (ሸ)
1. ሺንሺቾ ከተማ ( ደቡብ)
2. 06 ሕብረት (ድሬዳዋ)
3. ጫንጮ ከተማ (ኦሮሚያ)
4. አቃቂ ማዞሪያ (አ/አ)
………..
ነገ የሚካሄድ ጨዋታ
የጁፍሬ ወልድያ ከ ሾኔ ከተማ
በ8:00 ሰአት በወልድያ ሙሃመድ ሁሴን አላሙዲ ስታዲየም
እንደ ስላሴ ከ ያሶ ከተማ
በ10:00 ሰአት
በሸህ ሙሃመድ ሁሴን አላሙዲ ስታዲየም
የመክፈቻ ስነስርአቱ ከ 6:30 ይጀምራል!!
መልካቆሌ ላይ ጧት 2 ጨዋታወች ይካሄዳሉ!!
ሃገር አቀፍ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር የእጣ ማወውጣት ፕሮግራም ተካሄደ!!
Hatricksport team