ጨዋታው የፋሲል ከነማ ማለያ ከወልቂጤ ከተማ ማለያ ጋር ተመሳሳይነት ስላለዉ ለመለየት ምቹ አይደለም በዕለቱ ዋና ዳኛ ተካልኝ ለማ ተብሎ ከተያዘለት ሰአት 18 ደቂቃ ዘግይቶ ነበር የጀመረዉ።
በፋሲል ከነማ የተሻለ እንቅስቃሴ ጨዋታው መካሄድ የጀመረ ሲሆን በአንፃሩ በሁለቱም ቡድኖች በኩል ለጎል የቀረበ ኳስ በመሞከር ረገድ ደካማ እንቅስቃሴ ነበር ገና ከጅምሩ የተስተዋለዉ።
ሁለቱም ቡድኖች ጥንቃቄ የታከለበት ደካማ እንቅስቃሴ በማድረግ ጨዋታቸዉን ማካሄድ የቀጠሉ ሲሆን በወልቂጤዎች በኩል አስራት በግንባሩ ገጭቶ ወደ ዉጪ ከወጣችበት ኳስ ዉጪ ተጨማሪ ለጎል የቀረበ ሙከራ ማድረግ ያልቻሉ ሲሆን በፋሲሎች በኩል ሽመክት ጉግሳ ከርቀት ሞክሮ የግቡ ቋሚ ከመለሰበት ኳስ ዉጪ ተጨማሪ ሙከራዎች ሳይደረጉ የመጀመሪያው አጋማሽ 0-0 በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።
- ማሰታውቂያ -
ከዕረፍት መልስ ወልቂጤዎች ተመስገንን በፋሲል በመቀየር ጨዋታቸዉን ማድረግ የቀጠሉ ሲሆን ከመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለዉን ወልቂጤ ከተማን ገና ከጅምሩ ማሳየት ጀምረዋል።
ፋሲሎች በበኩላቸዉ አጀማመራቸዉ በመጠኑ የተቀዛቀዘ የነበረ ሲሆን በመልሶ ማጥቃት የግብ እድል ለመፍጠር ሙከራዎችን ሲያደርጉ ነበር።
ጨዋታዉ ወደ መገባደጃዉ አከባቢ ሲቃረብ ከመጀመሪያው በተሻለ መንገድ መነቃቃት የተፈጠረበት ሲሆን ለወልቂጤ ከተማዎች አቡበከር ሳኒ ለጎል የቀረበች ኳስ ሳይጠቀምበት የቀረዉ አጋጣሚ ለወልቂጤዎች የሚያስቆጭ አጋጣሚ የነበረ ሲሆን ለፋሲሎች በበኩሉ ማውሊ ገጭቶ የወጣበት እና እንዲሁም ዱላ ፋሪስን ሞክሯት ሳይጠቀምባት የቀራት ለጎል የቀረበች ኳስ ለፋሲሎች የሚያስቆጭ አጋጣሚ ነበር።
የጨዋታዉ መጠናቀቂያ ላይ በተሰጠዉ የጭማሪ ደቂቃ ላይ ለወልቂጤዎች ጌታነህ ከበደ ደጋግሞ ለጎል የቀረበ ኳስ መሞከር ቢችልም ሳይሳካለት ቀርቶ የእለቱ ጨዋታ ያለ ግብ 0-0 በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።