ጨዋታዉ ፈጠን ባለ እንቅስቃሴ በሁለቱም ቡድኖች በኩል የተጀመረ ሲሆን በአንፃሩ መድኖች የተሻሉ የነበረ ሲሆን ገና በጠዋቱ በሲሞን ፒተር በኩል ለግብ የቀረበ ኳስ የሞከሩበት እና በግቡ አግዳሚ የተመለሰባቸዉ አጋጣሚ የጨዋታዉ የመጀመሪያ ሙከራ ሆኖ ተጠቃሽ ነዉ።
መድኖች ደጋግመው ወደ ኢትዮጵያ ቡናዎች የግብ ክልል ማምራት የቻሉ ሲሆን በ24ኛዉ ደቂቃ መሪ መሆን የቻሉበትን ጎል በወገኔ ገዛኸኝ በኩል አስቆጥረዉ ጨዋታው ወደ 1-0 ማምራት ችሏል።
ጎሏ ከተቆጠረችባቸዉ በኋላ ኢትዮጵያ ቡናዎች ምላሽ ለመስጠት ወደፊት አዘንብለዉ ተጫዉተዉ ተደጋጋሚ ለጎል የቀረበ ሙከራ ቢያደርጉም ሳይሳካላቸዉ ቀርቶ የመጀመሪያው አጋማሽ በመድህን 1-0 መሪነት ተጠናቋል።
- ማሰታውቂያ -
ከእረፍት መልስ ኢትዮጵያ ቡናዎች ጫላ ተሺቴን በአንተነህ ተፈራ የቀየሩ ሲሆን ይበልጥ የማጥቃት አጨዋወትን ለመከተል ጥረት ሲያደርጉ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን የመድህኖችን ጫና ለመቋቋም የከበዳቸዉ ይመስሉ ነበር።
በ52ኛዉ ደቂቃ የመድህኖቹ ወገኔ ገዛኸኝ ወደ ጎል የመታትን ኳስ የኢትዮጵያ ቡናዎች ኃይለሚካኤል አደፍርስ ተደርቦ ነክቷት በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሯት ጨዋታዉ በመድህን መሪነት ወደ 2-0 ተሸጋግሯል።
ጨዋታዉ በመድህን 2-0 መሪነት የቀጠለ ሲሆን የመጨረሻዎቹን ደቂቃዎች ኢትዮጵያ ቡናዎች ይበልጡን ተነቃቅተዉ ጎል ለማስቆጠር ወደ መድህኖች የግብ ክልል አዘንብለዉ ተደጋጋሚ ሙከራ እያደረጉ መጫወት የቻሉ ሲሆን በ82ኛዉ ደቂቃ ለኢትዮጵያ ቡናዎች ሮቤል ተክለሚካኤል ጎል አስቆጥሮ ጨዋታው በመድህኖች 2-1 አሸናፊነት ተጠናቋል።