By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ” ከዋሊያዎቹ ውጤት መጥፋት ጋር ተያይዞ ሃላፊነቱን የሚወስደው መልቀቂያ ያቀረበው ወገን ነው” አቶ ባህሩ ጥላሁን / የኢት.እግር ኳስ ፌዴ ዋና ስራ አስፈጻሚ/
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

” ከዋሊያዎቹ ውጤት መጥፋት ጋር ተያይዞ ሃላፊነቱን የሚወስደው መልቀቂያ ያቀረበው ወገን ነው” አቶ ባህሩ ጥላሁን / የኢት.እግር ኳስ ፌዴ ዋና ስራ አስፈጻሚ/

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 6 months ago
Share
SHARE

” ሁለቱ ጨዋታዎች ትርጉም ባይኖራቸውም
ብሄራዊ ቡድኑ ግን ይቀጥላል”
ኢንስትራክተር ዳንኤል ገ/ ማሪያም
/የዋሊያዎቹ ጊዜያዊ አሰልጣኝ/

“የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለብሄራዊ ቡድኑ የሚጠበቅበትን በማድረጉ ከዋሊያዎቹ ውጤት መጥፋት ጋር ተያይዞ ሃላፊነቱን የሚወስደው መልቀቂያ ያቀረበው ወገን ነው” ሲል የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።

የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ባህሩ ጥላሁን እንደተናገሩት “ፌዴሬሽኑ የሚጠበቅበትን አድርጓል ጥሩ ስታዲየም አስፈላጊ አቅርቦትና የሚፈለገውን በጀት በማቅረቡ ሀላፊነቱን ተወጥቷል ከዋሊያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ መሆን ጋር ተያይዞ ሃላፊነቱን የሚወስደው መልቀቂያ ያቀረበው ወገን ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

ስለ አሰልጣኞቹ የቅጥር ሂደት የተናገሩት ዋና ስራ አስፈጻሚው “አሰልጣኛቹን የሾምነው በጊዜያዊነት ነው ከማላዊ ፣ በአሜሪካ ጉዞ ላይ ለሚኖረው ጨዋታና ከግብጽ ብሄራዊ ቡድን ግን እስካለው ጨዋታ ድረስ ይመራሉ የደመወዝ ክፍያ የለውም በፌዴሬሽኑ የሚፈጸምላቸው ክፍያዎች ግን ይኖራሉ ከቋሚ አዲስ አሰልጣኝ ቅጥር ጋር ተያይዞ በቀጥይ አዲስ አሰልጣኝ የመሾም እቅድ ይዘን እየሰራን ነው ለአሁኑ ግን አንቸኩልም…” ሲሉ ገልጸዋል።

- ማሰታውቂያ -

ስለ ሞዛምቢክ ስታዲየም መስተንግዶ ምርጫ የተጠየቁት አቶ ባህሩ ጥላሁን ” ሱዳንን ብናይ በውስጥ ጉዳይዋ በመታመሷ ታንዛኒያም ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም ቢኖርም ሜዳው ተደጋጋሚ ውድድር በማስተናገዱ እየተጎዳ በመሆኑ ተከለከልን በመጨረሻም የሞዛቢክ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ከፌዴሬሽናችን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጋር ባላቸው አግባብ ተፈቅዶልን ቀድሞ የተጠየቅነው 12 ሺህ ብር ቅናሽ ተደርጎልን 8 ሺህ ብር እንድንከፍል ተስማምተናል አሁንም ቡድኑ ከሀገር ውጪ በመጫወቱ ዋጋ እየከፈለ ያለው ፌዴሬሽኑ ነው ባለሜዳ በመሆናችን ሌሎች ወጪዎችም ከፌዴሬሽኑ ካዝና የሚወጣ ነው” ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ባህሩ “ከተጨዋቾች ምርጫ ጋር ተያይዞ ለብሄራዊ ቡድን አልጫወትም ማለት በዲሲፕሊን መመሪያው መሰረት ቅጣት ይኖረዋል.. ነገር ግን የዝግጁነት ጥያቄ የተነሳበት እንጂ አልመጣም ያለ ተጨዋች እስካሁን አልገጠመንም” በማለት ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ከማላዊና ከግብጽ አቻቸው ጋር ለመርሀግብር ማሟያ የማጣሪያ ጨዋታ የሚያደርጉት የዋሊያዎቹ ስብስብ ከ41 ተጨዋቾች 23ቱን በመያዝ ጠንካራ ልምምድ መስራታቸውን አሰልጣኙ ተናገሩ።

ጊዜያዊው የዋሊያዎቹ አሰልጣኝ ዳንኤል ገ/ማሪያም በፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት በመገኘት በሰጡት መግለጫ “ልምድ ያላቸውን ተጨዋቾች ለማካተት ሞክረናል…ጌታነህ ከበደ ዝግጁ አለመሆኑን አቡበከር ናስር በጉዳት ዳዋ ሁቴሳም ከጉዳቱ እንዲያገግም እንዲያርፍ በማሰብ ሳይካተቱ ቀርተዋል ከ41 ተጨዋቾች 23ቱን መርጠን ጠንካራ ዝግጅት አድርገን ለማላዊ ጨዋታ ተዘጋጅተናል” ሲሉ ገልጸዋል።

” ከአሰልጣኝነቴ ውጪ የቴክኒክ ዳይሬክተር በመሆኔ ታዳጊዎች ሀገራቸውን ለረጅም ጊዜ እንዲያገለግሉ በማሰብ ወጣቶቹን ጠርተናቸዋል ለመጀመሪያ ጊዜም የተጠሩ ለነገ ተስፋ የሚጣልባቸው ተጨዋቾችን መርጠን አካተን ልምድ ካላቸው ጋር አዋህደን ለማላዊ ጨዋታ ተዘጋጅተናል” ሲሉ አሰልጣኝ ዳንኤል ተናግረዋል።

ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ዙሪያ የተጠየቁት አሰልጣኙ “ትላንት ለነበረው የወዳጅነት ጨዋታ ቀድመን የፈለግነው ወላይታ ድቻን ቢሆንም እረፍት በመሆናቸው ከአርባ ምንጭ ጋር ልንጫወት ችለናል ጨዋታው ደግሞ አቋም መመልከቻ ቡድን ማዋቀሪያ እንጂ የውጤት አይደለም” ሲሉ መልሰዋል።

” ከኮትዲቯር የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ በመሆናችን ጨዋታዎቹ ትርጉም ላይኖራቸው ይችላል ብሄራዊ ቡድኑ ግን ይቀጥላል ” ያሉት አሰልጣኝ ዳንኤል ገ/ ማሪያም
” የመርሃግብር ማሟያ የሆነና ትርጉም የሌለው ጨዋታን መምራት ቢከብድም በዚህ መሰሉ ጨዋታ ላይ እድል አግኝቶ ቡድን መምራትም ጥንካሬነው” ሲሉ መልሰዋል።

ከአፍሪካ ዋንጫ ውጪ የሆኑት ዋሊያዎቹ ሞዛምፒክ መዲና ማፑቶ ላይ የፊታችን ማክሰኞ የማላዊ ብሄራዊ ቡድንን ያስተናግዳሉ።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ” ለሀገር ዉስጥ በረኞች ትኩረት ለሚሰጡ አሰልጣኞች ትልቅ ክብር አለኝ” መክብብ ደገፉ /የሲዳማ ቡና ግብ ጠባቂ/
Next Article ካፍ ስታዲየሞቻችን ማገዱ ያስከተለው ከፍተኛ ወጪ….. ዋሊያዎቹ የፊታችን ማክሰኞ ከማላዊ አቻቸው ጋር ላለባቸው የመርሀ ግብር ማሟያ  ጨዋታ  ነገ  ወደ ሞዛምፒክ መዲና ማፑቶ ያቀናሉ…

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አሰራሩን ለማዘመን ስምምነት ተፈራርሟል

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 2 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከበርካታ ጨዋታዎች በኋላ አሸንፏል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 24ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !
የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ጨዋታዎች /LIVESCORE/
ወላይታ ድቻ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች አስፈርሟል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?