ሞቅ ባለ በጥሩ ፉክክር የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ የጀመረ ሲሆን ገና ከጅምሩ ሀዋሳ ከነማዎች በሙጂብ ቃሲም በኩል ለጎል የሚሆን ኳስ ሞክረዉ በመቻሎች የግብ ዘብ ዉበሸት ጭላሎ ተመልሶባቸዋል።
እንዲሁም መቻሎች የቅጣት ምት ኳስ አግኝተዉ ዳዊት ወርቁ ወደ ግብ አክርሮ የመታ ሲሆን በከነማዎቹ የግብ ዘብ መሐመድ ሙንታሪ የተመለሰበት ተጠቃሽ ነዉ።
- ማሰታውቂያ -
የሁለቱ ክለቦች እንቅስቃሴ ተመጣጣኝ የነበረ ሲሆን በአንፃሩ ለጎል የቀረቡ ኳሶችን በመሞከር ረገድ መቻሎች የተሻሉ ነበሩ። ለአብነትም መቻሎች በግርማ ዲሳሳ ፣ ሳሙኤል ሳሊሶ እና እስራኤል እሼቱ በኩል ያደረጓቸዉ ለጎል የቀረቡ ሙከራዎች ተጠቃሾች ናቸዉ።
ከእዛ በኋላ በሁለቱም ክለቦች በኩል ተጨማሪ ለጎል የሚሆኑ ኳሶች ሙከራ ሳይደረገ የመጀመሪያዉ አጋማሽ 0-0 በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።
ከእረፍት መልስ ገና ከጅምሩ ለሀዋሳ ከነማዎች ተባረክ ሄፋሞ በ46ኛ ደቂቃ በግንባሩ ገጭቶ ኳሷን ከመረቡ ጋር በማገናኘት ሀይቆቹን 1-0 በሆነ ዉጤት መሪ ማድረግ ችሏል።
መቻሎች ጎሏ ከተቆጠረችባቸዉ በኋላ ዉጤቱን ለመቀየር ወደፊት አዘንብለዉ አጥቅተዉ መጫወትን ምርጫቸዉ ያደረጉ ሲሆን በሳሙኤል ሳሊሶ በኩል ያደረጉት ለጎል የቀረበ ኳስ በከነማዎቹ ግብ ጠባቂ የተመለሰባቸዉ ተጠቃሽ ነዉ።
ሀዋሳ ከነማዎች ዉጤቱን አስጠብቀዉ ለመዉጣት የጀርባ ክፍላቸዉን በማጠናከር ጥንቃቄ የታከለበትን ጨዋታ እያደረጉ እስከ መጨረሻዉ ደቂቃ አከባቢ ድረስ ቢጓዙም ባለቀ ሰአት መቻሎች መደበኛዉ የጨዋታ ክፍለ ግዜ ተጠናቆ በተሰጠዉ የጭማሪ ደቂቃ 90+5 ላይ ምንተስኖት አዳነ ጎል አስቆጥሮ የእለቱ ጨዋታ 1-1 በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።
ሀዋሳ ከነማዎች ከጨዋታዉ መጠናቀቅ በኋላ በእለቱ የጨዋታ ዋና ዳኛ ኤፍሬም ደበሌ ላይ ቅሬታቸዉን ሲያሰሙ ነበር።