በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ላይ በርካታ ጨዋታዎችን በአቻ ዉጤት በማጠናቀቅ የሚታወቁት ሀድያዎች የሊጉን መሪ መቻል ገጥመዉ ገና በመባቻዉ ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም ገና በ2ተኛዉ ደቂቃ አቤል ነጋሽ ከግራ በኩል ከከንዓን የተቀበለዉን ኳስ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መቻል መሪ ማድረግ ችሏል።
ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ በቶሎ መልስ ለመስጠት የሞከሩት ሀድያዎች በ7ተኛዉ ደቂቃ ላይ ዳዋ ሁቴሳ ከሀድያ የቀኝ ማጥቃት ሳሙኤል ያሻማዉን የቅጣት ምት ኳስ በጭንቅላቱ በመግጨት ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት ወጥታለች።
- ማሰታውቂያ -
በመልሶ ማጥቃት ከንዓን እየገፋ የሀድያ ሳጥን ውስጥ ከደረሰ በኋላ ያቀበለዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ግብ ጠባቂዉ ያሬድ መልሶበታል ። ቀስ በቀስ ወደ ጨዋታዉ ለመመለስ ጥረት የቀጠሉት ሀድያዎች በሳሙኤል ዮሐንስ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ከርቀት ቢያደርጉም ኳሷ የግቡን ቋሚ ገጮታ ተመልሳለች ። በ ደቂቃ ግን የግራ መስመር ተከላካዩ ሄኖክ አርፌጮ ያቀበለዉን ኳስ መለሰ ሚሻሞ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል።
ከዕረፍት መልስ በሙከራ ረገድ በተወሰኑ መልኩ የተቀዛቀዘ በነበረዉ ጨዋታም በ57ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሰመረ ሀፍተይ ግሩም ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት አማካዩ ከነዓን ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መቻል ዳግም መሪ ማድረግ ችሏል። ከፍፁም ቅጣት ምቷ በኋላም በ70ኛዉ ደቂቃ ከግራ መስመር በኩል ሄኖክ አርፌጮ ከቅጣት ምት በቀጥታ ያቀበለዉን ኳስ ግሩም ሀጎስ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሮ ሀድያ ሆሳዕና አቻ መሆን ችሏል ።
አቻ ከሆኑ በኋላ አሸናፊ የሚያደርጋቸውን ጎል ለማግኘት ጥረት ማድረግ በቀጠሉት ሁለቱም ክለቦች በመጨረሻም ሀድያዎች በ86ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሀድያዎች ድንቅ ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም ከአጥቂዉ ዳዋ ሁቴሳ የተቀበለዉን ኳስ ተመስገን ብርሐኑ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አሸናፊ ማድረግ ችሏል።
– አፄዎቹ ከመመራት ተነስተዉ ሀዋሳ ከተማን ሁለት ለአንድ በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል ።
ከሙከራዎች ይልቅ ሀይልን ቀላቅሎ በመጫወት እና በርካታ ካርዶችን ባስመለከተዉ የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ ገና በ7ተኛዉ ደቂቃ ላይ ቸርነት አዉሽ ድንቅ የግብ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም የግብ ዘቡ ይድነቃቸው መልሶበታል። ከዚች የጨዋታው የመጀመሪያ ሙከራ በመቀጠልም በ12ተኛዉ ደቂቃ ላይ የመስመር ተጫዋቹ ቸርነት ጉግሳ ከጌታነህ የተቀበለዉን ኳስ ከርቀት ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ፅዮን ኳሷን መልሷል።
ምንም እንኳን ቶሎ ቶሎ የተጋጣሚ ቡድን ሳጥን ውስጥ በመድረስ አፄዎቹ ይሻሉ እንጅ በሙከራ ረገድ ደካማ በነበረዉ የመጀመሪያው አጋማሽ በ41ኛዉ ደቂቃ ላይ ሀዋሳዎች መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም በግራ በኩል ከተባረክ ሄፋሞ የተሻገረለትን ኳስ የቀድሞዉ የአፄዎቹ አማካይ ታፈሰ ሰለሞን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።
ከዕረፍት መልስ የተጫዋቾችን ለዉጥ በማድረግ በይበልጥ ጨዋታዉን ለመቆጣጠር ጥረት ያደረጉት አፄዎቹ በ50ኛዉ ደቂቃ ላይ ተቀይሮ በገባዉ ቃልኪዳን ዘላለም አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ማድረግ ቢችሉም ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች ።
ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ማድረግ የቀጠሉት አፄዎቹ ውጥናቸዉ ሰምሮ በ76ተኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አግኝተዋል ፤ በዚህም አምበሉ ጌታነህ ከበደ ያሻማዉን የቅጣት ምት ኳስ ተጨራርፋ ያገኛት አማኑኤል ገ/ሚካኤል ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን አቻ አድርጓል። ከዚች ግብ በኋላ ከመከላከሉ በመጠኑ ሙከራዎችን ለማድረግ ጥረት የጀመሩት ሀዋሳዎች በተከላካዩ በረከት አማካኝነት ሙከራ ማድረግ ቢችሉም ነገር ግን በ88ተኛዉ ደቂቃ ላይ ጌታነህ ከበደ ያሻማዉን ኳስ ቃልኪዳን ዘላለም ወደ ግብነት ቀይሮ ሀዋሳን አሳዛኝ ተሸናፊ ፋሲልን ደግሞ አሸናፊ ማድረግ ችሏል ።