By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ መድኅን እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዳማ ከተማኢትዮጵያ መድህንዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ መድኅን እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 10 months ago
Share
SHARE

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ተጀምረዋል ።

በቀዳሚነት ከቀን 10:00 ጀምሮ የተደረገው የኢትዮጵያ መድኅን እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል ።

በጨዋታው በኢትዮጵያ መድኅን በኩል የነበረው የመጀመሪያ ምርጥ 11 ይህን ይመስላል ። አቡበከር ኑራ ፣ አብዱልከሪም መሀመድ ፣ ተካልኝ ደጀኔ ፣ ሐቢብ መሀመድ ፣ አስጨናቂ ፀጋዬ ፣ አሚር ሙደሲር ፣ ሀብታሙ ሸዋለም ፣ ባሲሩ ኡመር ፣ ሐቢብ ከማል ፣ ኪቲካ ጀማ እና ሲሞን ፒተር ።

በአዳማ ከተማ በኩል የነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍም እንደሚከተለው ነው ። ሰይድ ሀብታሙ ፣ ጀሚል ያዕቆብ ፣ ሚሊዮን ሰለሞን ፣ አዲስ ተስፋዬ ፣ ደስታ ዮሀንስ ፣ አማኑኤል ጎበና ፣ መስዑድ መሀመድ ፣ ዳንኤል ደምሴ ፣ አብዲሳ ጀማል ፣ አሜ መሀመድ እና ቦና አሊ ናቸው ።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ሁለተኛ ላይ የተቀመጠው ኢትዮጵያ መድኅን ወደ መሪነቱ ለመመለስ ጨዋታውን ያደረገ ሲሆን ገና በ10ኛው ደቂቃ ላይ ቀዳሚ መሆን ችሏል ።

ሲሞን ፒተር ከሳጥን ውጪ የመታውን ኳስ ግብ ጠባቂው ሰይድ ሀብታሙ ሲተፋው በቅርብ የነበረው ሐቢብ ከማል ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

አዳማ ከተማዎች በቀጣዮቹ ደቂቃዎች የተሻለ ለመንቀሳቀስ ጥረቶችን ያደረጉ ሲሆን በተደጋጋሚ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል መድረስም ችለዋል ።

በ36ኛው ደቂቃ ላይ አዳማ ከተማ ወደ አቻነነት ተመልሷል ። አሜ መሀመድ ከቀኝ መስመር ያሻገረውን ኳስ ቦና አሊ አግኝቶ በፍፁም መረጋጋት ኳሱን ከመረብ ላይ አሳርፏል ።

በቀሪዎቹ የመጀመሪያ አጋማሽ ደቂቃዎች ላይ ኢትዮጵያ መድኅኖች በተወሰኑ አጋጣሚዎች ዳግም ወደ መሪነት ለመመለስ ጥረቶችን ያደረጉ ሲሆን በአዳማ ከተማ በኩል ግን እጅግ ያለቀላቸው ኳሶችን አግኝተው ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ።

በ37ኛው ደቂቃ ላይ ኪቲካ ጀመረ በቀኝ የሳጥኑ አቅጣጫ ከአዲስ ተስፋዬ ጋር ታግሎ ይዞ የገባውን ኳስ ለመቀነስ ጥረት ቢያደርግም የደረሰበት ተጫዋች አልነበረም ። ከአራት ደቂቃዎች በኋላም ግብ አስቆጣው ሐቢብ ከማል በረጅም የደረሰውን ኳስ ለመጠቀም ሲሞክር የአዳማ ከተማው ግብ ጠባቂ ሰይድ ሀብታሙ ከግቡ ወጥቶ እንዳይጠቀምበት አድርጓል ።

ከአንድ ደቂቃ በኋላ ቦና አሊ የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ የዕለቱ ኮከብ የነበረው አቡበከር ኑራ መልሶበታል ። የአቡበከር ድንቅ ብቃት ዳግም በታየበት ሌላ የግብ ሙከራ ምልሰት አብዲሳ ከማል በግሩም ሁኔታ ከሳጥን ውጪ ወደ ግብ የመታውን ኳስ ግቡ ላይ እንዳይቆጠር ማድረግ ችሏል ።

በ44ኛው ደቂቃ ላይ ዳግም አብዲሳ ጀማል እና አቡበከር ኑራ በተገናኙበት የግብ ሙከራ አዳማ ከተማ መሪ ሆነ ተብሎ ቢጠበቅም አቡበከር ግቡን ለሁለተኛ ጊዜ ሳያስደፍር የመጀመሪያው አጋማሽ እንዲጠናቀቅ አድርጓል ።

የሁለተኛው አጋማሽ ቀዳሚ ደቂቃዎች ላይ የአሰልጣኝ ይታገሱ ቡድን ወደ ግብ በተሻለ የመድረስ አዝማሚያ ቢያሳይም በ51ኛው ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ግብ አስተናግዷል ።

ሐቢብ ከማል በረጅም የተላከለትን ኳስ በሳጥን ውስጥ ሆኖ ለማስቆጠር ጥረት በሚያደርግበት ወቅት በሚሊዮን ሰለሞን ጥፋቶ ተሰርቶበት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ራሱ ሐቢብ ከመረብ አሳርፏል ። ጥፋቱን የሰራው ሚሊዮን ሰለሞን በበኩሉ በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል ።

በጨዋታው ሁለተኛ ግብ ያስቆጠረው ሐቢብ ከማል በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች ሰባት አድርሷል ።

ከግቡ በኋላ የአሰልጣኝ ፀጋዬ ገብረመድህን ቡድን ኳሱን ተቆጣጥሮ ለመጫወት የቻለ ሲሆን ወደ አዳማ ከተማ ግብ ቀርቦ የግብ ሙከራ ከማድረግ አንፃር ግን ያን ያህል ነበሩ ።

በአንፃሩ የቁጥር ብልጫ የተወሰደባቸው አዳማ ከተማዎች በጥቂት አጋጣሚዎች የተጋጣሚያቸውን የግብ ክልል ለመፈትሽ ሞክረዋል ።

በ69ኛው ደቂቃ ላይ ግብ አስቆጣሪው ቦና አሊ ከመስዑድ መሀመድ የደረሰውን ኳስ ከሳጥን ውስጥ ሆኖ ወደ ግብ መሞከር ቢችልም ግብ ጠባቂው በቀላሉ አድኖበታል ።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ ሊጠናቀቅ ስምንት ያህል ደቂቃዎች ሲቀሩት አዳማ ከተማዎች ዳግም ወደ አቻነት የተመለሱበትን ግብ አስቆጥረዋል ።ተቀይሮ የገባው አድናን ረሻድ ኳስ እና መረብን ያገናኘው ተጫዋች ነው ።

ቀሪዎቹ የመጨረሻ ደቂቃዎች በሁለቱም በኩል ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ይዞ ለመውጣት ጥረቶች የተደረጉበት ሲሆን በተለይም በ90+3 ላይ ቢንያም አይተን ከሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ አክርሮ ወደ ግብ የመታው እና በአቡበከር ቸየመለሰው ኳስ ተጠቃሽ ነው ።

በመጨረሻም ጨዋታው 2 – 2 ተጠናቋል ።

ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ መድኅን በ27 ነጥቦች ዳግም ወደ ሊጉ መሪነት ሲመለስ አዳማ ከተማ በበኩሉ በ15 ነጥቦች በነበረበት 12ኛ ደረጃ ለመቆየት ተገዷል ።

ከጨዋታዉ በኋላ አስተያየታቸውን የሰጡት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ በጨዋታው የነበራቸው እንቅስቃሴ ጥሩ አለመሆኑን በመግለፅ በርካታ ኳሶችን ያዳነውን ግብ ጠባቂውን አቡበከር ኑራን አድንቀዋል ። በአንፃሩ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ የመከኑት ኳሶች ዋጋ እንዳስከፈላቸው ተናግረዋል ።

በጨዋታው የነበሩ ቁጥራዊ መረጃዎች

ኢትዮጵያ መድኅን 2 – 2 አዳማ ከተማ

          10 የግብ ሙከራ 15
           6 ኢላማቸውን የጠበቁ 9
              10 ጥፋት 16
               0 ቢጫ ካርድ 4
               0 ቀይ ካርድ 1
               4 የማዕዝን ምት 9
           52% የኳስ ቁጥጥር 42%

ቀጣይ የ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች
ሐሙስ የካቲት 16 (ምሸት 1:00)
አዳማ ከተማ ከ ወልቂጤ ከተማ
አርብ የካቲት 17 (ቀን 10:00)
ሀድያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ መድኅን

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የኢት.ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዳኞች ታውቀዋል
Next Article አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ኢትዮጵያ ቡና ላይ ያቀረበው ክስ ውድቅ ሆነ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከነማ

ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የፋሲል ከነማን ይግባኝ ውድቅ አደረገ

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 6 months ago
​የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ
“ከጊኒ ጋር በሚኖረን ጨዋታ ከተሳካ 6 ነጥብ ካልሆነ ግን 4 ነጥብ ለማግኘት እንጥራለን” አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
ሴራሊዮን ከኢትዮጵያ ጋር ላለባት ጨዋታ ለ35 ተጨዋቾችዋ ጥሪ ኣቀረበች
የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ እርዳታ ዛሬ አስረከቡ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?