መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ መድኅን እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዳማ ከተማኢትዮጵያ መድህንዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ መድኅን እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

አጋራ
አጋራ

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ተጀምረዋል ።

በቀዳሚነት ከቀን 10:00 ጀምሮ የተደረገው የኢትዮጵያ መድኅን እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል ።

በጨዋታው በኢትዮጵያ መድኅን በኩል የነበረው የመጀመሪያ ምርጥ 11 ይህን ይመስላል ። አቡበከር ኑራ ፣ አብዱልከሪም መሀመድ ፣ ተካልኝ ደጀኔ ፣ ሐቢብ መሀመድ ፣ አስጨናቂ ፀጋዬ ፣ አሚር ሙደሲር ፣ ሀብታሙ ሸዋለም ፣ ባሲሩ ኡመር ፣ ሐቢብ ከማል ፣ ኪቲካ ጀማ እና ሲሞን ፒተር ።

በአዳማ ከተማ በኩል የነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍም እንደሚከተለው ነው ። ሰይድ ሀብታሙ ፣ ጀሚል ያዕቆብ ፣ ሚሊዮን ሰለሞን ፣ አዲስ ተስፋዬ ፣ ደስታ ዮሀንስ ፣ አማኑኤል ጎበና ፣ መስዑድ መሀመድ ፣ ዳንኤል ደምሴ ፣ አብዲሳ ጀማል ፣ አሜ መሀመድ እና ቦና አሊ ናቸው ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ሁለተኛ ላይ የተቀመጠው ኢትዮጵያ መድኅን ወደ መሪነቱ ለመመለስ ጨዋታውን ያደረገ ሲሆን ገና በ10ኛው ደቂቃ ላይ ቀዳሚ መሆን ችሏል ።

ሲሞን ፒተር ከሳጥን ውጪ የመታውን ኳስ ግብ ጠባቂው ሰይድ ሀብታሙ ሲተፋው በቅርብ የነበረው ሐቢብ ከማል ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

አዳማ ከተማዎች በቀጣዮቹ ደቂቃዎች የተሻለ ለመንቀሳቀስ ጥረቶችን ያደረጉ ሲሆን በተደጋጋሚ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል መድረስም ችለዋል ።

በ36ኛው ደቂቃ ላይ አዳማ ከተማ ወደ አቻነነት ተመልሷል ። አሜ መሀመድ ከቀኝ መስመር ያሻገረውን ኳስ ቦና አሊ አግኝቶ በፍፁም መረጋጋት ኳሱን ከመረብ ላይ አሳርፏል ።

በቀሪዎቹ የመጀመሪያ አጋማሽ ደቂቃዎች ላይ ኢትዮጵያ መድኅኖች በተወሰኑ አጋጣሚዎች ዳግም ወደ መሪነት ለመመለስ ጥረቶችን ያደረጉ ሲሆን በአዳማ ከተማ በኩል ግን እጅግ ያለቀላቸው ኳሶችን አግኝተው ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ።

በ37ኛው ደቂቃ ላይ ኪቲካ ጀመረ በቀኝ የሳጥኑ አቅጣጫ ከአዲስ ተስፋዬ ጋር ታግሎ ይዞ የገባውን ኳስ ለመቀነስ ጥረት ቢያደርግም የደረሰበት ተጫዋች አልነበረም ። ከአራት ደቂቃዎች በኋላም ግብ አስቆጣው ሐቢብ ከማል በረጅም የደረሰውን ኳስ ለመጠቀም ሲሞክር የአዳማ ከተማው ግብ ጠባቂ ሰይድ ሀብታሙ ከግቡ ወጥቶ እንዳይጠቀምበት አድርጓል ።

ከአንድ ደቂቃ በኋላ ቦና አሊ የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ የዕለቱ ኮከብ የነበረው አቡበከር ኑራ መልሶበታል ። የአቡበከር ድንቅ ብቃት ዳግም በታየበት ሌላ የግብ ሙከራ ምልሰት አብዲሳ ከማል በግሩም ሁኔታ ከሳጥን ውጪ ወደ ግብ የመታውን ኳስ ግቡ ላይ እንዳይቆጠር ማድረግ ችሏል ።

በ44ኛው ደቂቃ ላይ ዳግም አብዲሳ ጀማል እና አቡበከር ኑራ በተገናኙበት የግብ ሙከራ አዳማ ከተማ መሪ ሆነ ተብሎ ቢጠበቅም አቡበከር ግቡን ለሁለተኛ ጊዜ ሳያስደፍር የመጀመሪያው አጋማሽ እንዲጠናቀቅ አድርጓል ።

የሁለተኛው አጋማሽ ቀዳሚ ደቂቃዎች ላይ የአሰልጣኝ ይታገሱ ቡድን ወደ ግብ በተሻለ የመድረስ አዝማሚያ ቢያሳይም በ51ኛው ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ግብ አስተናግዷል ።

ሐቢብ ከማል በረጅም የተላከለትን ኳስ በሳጥን ውስጥ ሆኖ ለማስቆጠር ጥረት በሚያደርግበት ወቅት በሚሊዮን ሰለሞን ጥፋቶ ተሰርቶበት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ራሱ ሐቢብ ከመረብ አሳርፏል ። ጥፋቱን የሰራው ሚሊዮን ሰለሞን በበኩሉ በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል ።

በጨዋታው ሁለተኛ ግብ ያስቆጠረው ሐቢብ ከማል በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች ሰባት አድርሷል ።

ከግቡ በኋላ የአሰልጣኝ ፀጋዬ ገብረመድህን ቡድን ኳሱን ተቆጣጥሮ ለመጫወት የቻለ ሲሆን ወደ አዳማ ከተማ ግብ ቀርቦ የግብ ሙከራ ከማድረግ አንፃር ግን ያን ያህል ነበሩ ።

በአንፃሩ የቁጥር ብልጫ የተወሰደባቸው አዳማ ከተማዎች በጥቂት አጋጣሚዎች የተጋጣሚያቸውን የግብ ክልል ለመፈትሽ ሞክረዋል ።

በ69ኛው ደቂቃ ላይ ግብ አስቆጣሪው ቦና አሊ ከመስዑድ መሀመድ የደረሰውን ኳስ ከሳጥን ውስጥ ሆኖ ወደ ግብ መሞከር ቢችልም ግብ ጠባቂው በቀላሉ አድኖበታል ።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ ሊጠናቀቅ ስምንት ያህል ደቂቃዎች ሲቀሩት አዳማ ከተማዎች ዳግም ወደ አቻነት የተመለሱበትን ግብ አስቆጥረዋል ።ተቀይሮ የገባው አድናን ረሻድ ኳስ እና መረብን ያገናኘው ተጫዋች ነው ።

ቀሪዎቹ የመጨረሻ ደቂቃዎች በሁለቱም በኩል ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ይዞ ለመውጣት ጥረቶች የተደረጉበት ሲሆን በተለይም በ90+3 ላይ ቢንያም አይተን ከሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ አክርሮ ወደ ግብ የመታው እና በአቡበከር ቸየመለሰው ኳስ ተጠቃሽ ነው ።

በመጨረሻም ጨዋታው 2 – 2 ተጠናቋል ።

ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ መድኅን በ27 ነጥቦች ዳግም ወደ ሊጉ መሪነት ሲመለስ አዳማ ከተማ በበኩሉ በ15 ነጥቦች በነበረበት 12ኛ ደረጃ ለመቆየት ተገዷል ።

ከጨዋታዉ በኋላ አስተያየታቸውን የሰጡት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ በጨዋታው የነበራቸው እንቅስቃሴ ጥሩ አለመሆኑን በመግለፅ በርካታ ኳሶችን ያዳነውን ግብ ጠባቂውን አቡበከር ኑራን አድንቀዋል ። በአንፃሩ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ የመከኑት ኳሶች ዋጋ እንዳስከፈላቸው ተናግረዋል ።

በጨዋታው የነበሩ ቁጥራዊ መረጃዎች

ኢትዮጵያ መድኅን 2 – 2 አዳማ ከተማ

          10 የግብ ሙከራ 15
           6 ኢላማቸውን የጠበቁ 9
              10 ጥፋት 16
               0 ቢጫ ካርድ 4
               0 ቀይ ካርድ 1
               4 የማዕዝን ምት 9
           52% የኳስ ቁጥጥር 42%

ቀጣይ የ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች
ሐሙስ የካቲት 16 (ምሸት 1:00)
አዳማ ከተማ ከ ወልቂጤ ከተማ
አርብ የካቲት 17 (ቀን 10:00)
ሀድያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ መድኅን

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...