የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ ኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ን ያሰናበተው በተገቢው መንገድ ነው ሲል ወሰነ።
አሰልጣኙ ከውል ውጪ ተሰናብቻለሁ ዲሲፕሊን ኮሚቴ መብቴን ያስከብርልኝ በማለት ክስ ያቀረበ ሲሆን ዲሲፕሊን ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ ኢትዮጵያ ቡና ከአሰልጣኙ ጋር በውስጥ የተፈራረመውን ውል ፌዴሬሽን ሄደው ከፈረሙት ውል ጋር በጋራ በማጸደቁ የስንብት ርምጃው ተገቢነት ሲል ብይን መስጠቱ ታውቋል።
ብዙ ክለቦች ከአሰልጣኞች ጋር ውል ሲገቡ ከዋናው ውል ውጪ ውጤት ከጠፋ ስለሚሰናበትበት በስምምነት ስለሚለያዩበት የሚስማሙበትን ውል ፌዴሬሽን ሄደው ስለማያጸድቁ በራሳቸው ተስማምተው የፈረሙት የውስጥ ውል ውድቅ ሆነው በተደጋጋሚ ሲቀጡ መታየታቸውን የታዘበው የመረጃ ምንጩ በሊጉ የሚገኙ ክለቦች ከኢትዮጵያ ቡና ሊማሩ እንደሚገባ መክሯል።
ከሁለቱ ወገኖች አንደኛው ወገን ውል ማቋረጥ ከፈለገ ከአንድ ወር በፊት አስቀድሞ ተናግሮ ስምምነቱን ማቋረጥ ይቻላል በሚለውና በጸደቀው ውል መሠረት ለአሰልጣኝ ተመስገን ዳና ህዳር ላይ ውሉን አቋርጦ ከታህሳስ 1/2015 ጀምሮ እንዳሰናበተው ይታወሳል።