– ኢትዮጵያ ቡና ሲዳማ ቡናን ከድንቅ የጨዋታ ብልጫ ጋር ማሸነፍ ችሏል ።
ቀን 10 ሰዓት ሲል በጀመረዉ የ16ተኛዉ ሳምንት የመጨረሻ ዕለት ጨዋታ ድንቅ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የተመለከትን ሲሆን በሙከራ ረገድ ግን ቡናዎቹ የተሻሉ ሁነዉ ተስተዉሏል ፤ በዚህም ገና በመባቻዉ በ9ነኛዉ ደቂቃ ላይ አንተነህ ተፈራ ከመስፍን ታፈሰ የተቀበለዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ተከላካዩ ደስታ ዮሐንስ አውጥቶበታል። የጨዋታዉን የበላይነት መቆጣጠር የቻሉት ቡናማዎቹ ምንም እንኳን እንደነበራቸዉ ብልጫ ሙከራን ማድረግ ባይችሉም ከደቂቃዎች በኋላ በአብዱልከሪም ወርቁ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ማድረግ ችለዉ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት ወጥታለች ።
በአንፃሩ ቡናማዎቹ ትተዋቸዉ የሚሄዱ ክፍት ቦታዎችን ለመጠቀም ጥረት ሲያደርጉ የነበሩት ሲዳማ ቡናዎች አንድ ሁለት ሙከራዎችን ማድረግ ችለዉ የነበረ ቢሆንም ኢላማቸዉን ሳይጠብቁ ወጥተዉባቸዋል። ከዕረፍት መልስ የበላይነታቸዉን አጠናክረዉ የቀጠሉት ቡናማዎቹ በመስፍን ታፈሰ እና በፍቃዱ አለማየሁ አማካኝነት ከመስመር በተነሱ ኳሶች ድንቅ ሙከራዎች ማድረግ ችለዋል።
- ማሰታውቂያ -
አሁንም ተደጋጋሚ ሚከራዎችን ማድረግ የቀጠሉት ቡናማዎቹ በ63ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም አስራት ያቀበለዉን ኳስ አብዱልከሪም ወደ ግብ ሲሞክር ኳሷ የጊት ጋትን እግር ነክታ ወደ ግብ ተቀይራለች። ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ በ66ተኛዉ ደቂቃ ላይ በዳመነ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ማድረግ ችለዉ የነበሩት ሲዳማዎች ዳግም ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም በ74ተኛዉ ደቂቃ ላይ አብዱልከሪም ከብሩክ በየነ የተቀበለዉን ሰንጣቂ ኳስ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። በመጨረሻም በጨዋታው የበላይ የነበሩት ቡናማዎቹ በ85ተኛዉ ደቂቃ ላይ በዕለቱ ኮከብ የነበረዉ መስፍን ለብሩክ ያቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ ወደ ግብነት ቀይሮ ጨዋታዉ በቡና 3ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።
– በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዳግም የሊጉ መሪ መሆን የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል ።
በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ እንቅስቃሴ ገና በመባቻዉ በ3ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ተቆጥሮበታል። በዚህም ባሲሩ ዑመር ያቀበለዉን ኳስ የመስመር አጥቂዉ ኪቲካ ጀማ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን ገና በመባቻዉ መሪ ማድረግ ችሏል። ከግቧ መቆጠር ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ በድጋሚ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአዲስ ግደይ እና ቢኒያም ጌታቸው አማካኝነት እጅግ አስቆጭ ሙከራዎችን ማድረግ ችለዉ የነበረ ቢሆንም ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።
በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ተደጋጋሚ ጫና የተደረገባቸዉ እና ግብም የተቆጠረባቸዉ አዳማ ከተማዎች በ22ተኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አጊኝተዋል ። በዚህም የመስመር አጥቂዉ ቢኒያም አይተን ያቀበለዉን ኳስ ዮሴፍ ታረቀኝ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል። የአቻነት ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ ዳግም ግብ ለማስቆጠር መጫወት የቀጠሉት ባንኮች ከተደጋጋሚ ሙከራዎች በኋላ አጋማሹ ሊጠናቀቅ ሲል ዳግም መሪ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል ። በዚህም ከቀኝ በኩል የተሻማዉን ኳስ አጥቂዉ በረከት ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቦቹ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።
ከዕረፍት መልስ እንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁሉ የጨዋታውን ብልጫ መዉሰድ የቻሉት ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ከደቂቃዎች በኋላ በ63ተኛዉ ደቂቃ ላይ መሪነታቸዉን ወደ 3ለ1 ከፍ ያደረጉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም አጥቂዉ ቢኒያም ጌታቸዉ ከባንክ የቀኝ ማጥቃት በኩል ያገኘዉን ኳስ በቶሎ ወደ ግብ በመላክ ግቡን ለቆ ወጥቶ የነበረዉ ሰይድ ሀብታሙ ላይ ማስቆጠር ችሏል።
በጨዋታው የመጨረሻው ደቂቃዎች ላይ በተደጋጋሚ አደጋዎችን ለመፍጠር ጥረት ሲያርጉ የነበሩት አዳማ ከተማዎች እንደ ልፋታቸው ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ፤ በተቃራኒው አራተኛ ግብ ተቀይሮ በገባዉ ሳይመን ፒተር አማካኝነት ተቆጥሮባቸዉ መርሐግብሩ ፍፃሜዉን አጊኝቷል።