By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን ሲያሸንፍ ፤ ፋሲል ከነማም ከተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ተመልሷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችሲዳማ ቡናሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማ

ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን ሲያሸንፍ ፤ ፋሲል ከነማም ከተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ተመልሷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

ቀን 10:00 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ መሪነት በጀመረዉ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን ማሸነፍ ችሏል።

ገና በመባቻዉ በፊት መስመር አጥቂዉ ማይክል ኪፖሩቪ አንድ ሁለት ሙከራዎች በጀመረዉ መርሐግብር ሲዳማ ቡናዎች በ12ተኛዉ ደቂቃ ላይ ጥሩ ዕድል አጊኝተዉ ነበር ፤ በዚህም ይስሀቅ ካኑ ከበረኛ የተመለሰዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ግን ለጥቂት በግቡ አናት ላይ ስትወጣ ፤ በድጋሚ ይሄዉ ተጫዋች በዚሁ መስመር ላይ ከሳጥን ዉጭ አስገራሚ ሙከራ ማድረግ ቢችልም ነገር ግን ኳሷን የግቡ አግዳሚ መልሷታል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ ላይ በ22ተኛዉ ደቂቃ ግብ ተቆጥሯል ፤ በዚህም ይስሀቅ ካኑ ከበዛብህ መለዮ ጋር በአንድ ሁለት ጥሩ ቅብብል ሳጥን ውስጥ ከደረሱ በኋላ ይስሀቅ ካኑ ወደ ቀኝ ካመዘነዉ የሜዳዉ ክፍል በግሩም ሁኔታ ግብ አስቆጥሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ በተደጋጋሚ ወደ ሲዳማ ቡና የግብ ክልል መድረስ የጀመሩት ወላይታ ዲቻዎች ምንም እንኳን አደገኛ የሚባሉ ሙከራዎችን ማድረግ ላይ እምብዛም የነበሩ ባይሆኑም ፤ ነገር ግን በ24ተኛዉ ደቂቃ በአበባየሁ ሀጪሶ እና በ26ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ በብስራት አማካኝነት ጥሩ ጥሩ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ችለዋል ።

በ41ኛዉ ደቂቃ ላይም ዲቻዎች አስቆጭ ሙከራ አድርገዉ ነበር ፤ በዚህም ከግራ መስመር በኩል ባየ ገዛኸኝ ያቀበለዉን ኳስ ተጫዋቾች በተዘናጉበት ወቅት አጥቂዉ ቢኒያም ፍቅሬ ከሳጥን ዉጭ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኳሷን የግቡ አግዳሚ መልሷታል። ከዕረፍት መልስ በ55ተኛዉ ደቂቃ ላይ ማይክል ኪፖሩቪ ከግራ መስመር በኩል ኳሷን እየገፋ በነፃነት ሳጥን ዉስጥ ገብቶ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ የወጣችበት አጋጣሚ በሲዳማዎች በኩል የተደረገች አስቆጭ ሙከራ ነበረች ።

በድጋሚ በ60ኛዉ ደቂቃ ላይ ማይክል ኪፖሩቪ ከቀኝ መስመር በኩል ወደ ሳጥን ያሻማዉን ኳስ በዛብህ መለዮ በጭንቅላቱ በመግጨት ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ግብ ጠባቂዉ ኳሷን እንደምንም ተቆጣጥሯል። ከዚች ሙከራ ከአንድ ደቂቃ በኋላም በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ ይስሀቅ ከሳጥን ዉጭ ድንቅ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ግን ለጥቂት ወጥታለች። የአቻነት ግብ ለማግኘት መታተር የቀጠሉት ዲቻዎች በ72ተኛዉ ደቂቃ ላይ በቢኒያም ፍቅሬ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ማድረግ ቢችሉም ነገር ግን የግቡ ቋሚ ሲከለክላቸዉ ፤ በ74ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን ሲዳማዎች በማይክል ኪፖሩቪ አማካኝነት ሁለተኛ ግብ አስቆጥረዉ ጨዋታዉን ሁለት ለዜሮ በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ሀድያ ሆሳዕናን ማሸነፍ ችሏል።

አመሻሽ 12:00 ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ዳንኤል ይታገሱ ፊሽካ በጀመረዉ ጨዋታ ገና በጊዜ ብልጫ በነበራቸዉ አፄዎቹ በኩል ፍቃዱ አለሙ ድንቅ ሙከራ ማድረግ ቢችም ግብ ጠባቂዉ ፔፔ አልዛየር ኳሷን በቀላሉ ተቆጣጥሯል። በአብዝሀኛዉ የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ወደ ራሳቸዉ የግብ ክልል አፈግፍገዉ በመጫወት ላይ የነበሩት ሀድያዎች በዳዋ ሆቴሳ እና ብሩክ ማርቆስ ጥሩ ጥሩ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ከቻሉ በኋላ በ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም እዮብ ማትያስ ለቡድን አጋሩ ለማቀበል የሞከረዉን ኳስ በስህተት ለዳዋ ሆቴሳ አቀብሎት ተጫዋቹ ዳዋ ደግሞ በግሩም ሁኔታ ኳሷን ከሳጥን ዉጭ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

ከዕረፍት መልስ የተጫዋች ቅያሪ በማድረግ ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን ግብ ለማግኘት ጥረት ማድረግ የጀመሩት አፄዎቹ ከብዙ ጥረቶች በኋላ በ65ተኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም ከግራ መስመር በኩል ሽመክት ያሻገረዉን ኳስ ጃቢየር ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን ወደ ጨዋታዉ መመለስ ችሏል ። አቻ ከሆነ በኋላ በይበልጥ ተጭነዉ መጫወት የቀጠሉት አፄዎቹ በ80ኛዉ ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተገኘዉን ኳስ ሽመክት ጉግሴ አሻምቶ ጋቶች ፓኖም ከጨረፈዉ በኋላ ያገኘዉ ምኞት ደበበ ወደ ግብነት በመቀየር በመርሐግብሩ አፄዎቹ ወሳኝ ሶስት ነጥብ እንዲይዙ አስችሏል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የፕሪሚየር ሊጉ የዳኞች ምደባና የዳኞቹ ውጤት ለዋጭ ስህተት አነጋጋሪ ሆኗል…
Next Article መቻል በምንይሉ ወንድሙ ሀትሪክ ታግዞ ወልቂጤ ከተማን ሲረታ ፤ ሀዋሳ ከተማም ቅዱስ ጊዮርጊስን ማሸነፍ ችሏል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችCovid-19

የኢትዮጵያ ቡና ተጨዋቾች ዛሬ የኮቪድ ምርመራ ይደረግላቸዋል

መሸሻ ወልዴ By መሸሻ ወልዴ 5 years ago
ድሬዳዋ ከተማ እና ወላይታ ዲቻ የድሬዳዋ ቆይታቸዉን በድል ደምድመዋል !!
የጅማ አባጅፋር ተጫዋቾች ወደ ክስ ሊያመሩ ነዉ !!
ባህርዳር ከተማዎች አዲስ አንበሎች ሾመዋል !!
የኢንተርሚዲየሪ /ሶስተኛ ወገን/ፈቃድ ህጋዊነት ነሃሴ 30/2013 ያበቃል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?