By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የድሬዳዋ ከተማ የመጨረሻ ቆይታ በሆነዉ የዕለቱ ጨዋታ መቻል እና ኢትዮጵያ ቡና አቻ ሲለያዩ ፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወሳኝ ድል አሳክቷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባመቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

የድሬዳዋ ከተማ የመጨረሻ ቆይታ በሆነዉ የዕለቱ ጨዋታ መቻል እና ኢትዮጵያ ቡና አቻ ሲለያዩ ፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወሳኝ ድል አሳክቷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በዕለቱ የመጀመሪያ መርሐግብር መቻል ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።

ቀን 10:00 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ሀይለየሱስ ባዘዘ ፊሽካ በጀመረዉ የዕለቱ ጨዋታ ገና በመባቻዉ ቡናማዎቹ መነሻዉን ከአማኑኤል አድማሱ ባደረገ ኳስ በመስፍን ታፈሰ አማካኝነት ድንቅ የግብ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። ከዚህ ሙከራ ከደቂቃዎች በኋላም ቡናማዎቹ በአንተነህ ተፈራ አማካኝነት በ9ነኛዉ ደቂቃ ላይ ድንቅ ሙከራ ካደረጉ በኋላ በዚያዉ ኳስ የተገኘዉን የማዕዘን ኳስ ዋሳዋ ጂኦፍሬ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኳሷን የግቡ ቋሚ መልሷታል።

በዚህ ሂደት በጀመረዉ ጨዋታ መቻሎች በሂደት ወደ ጨዋታዉ ገብተዉ በ20ኛዉ ደቂቃ ላይ ጨዋታዉን መምራት ጀምረዋል ፤ በዚህም ሳጥን ዉስጥ ምንይሉ ወንድሙ ግብ ጠባቂዉን ለማለፍ በሚሞክርበት ወቅት የተሰራበት ጥፋት ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት ራሱ ተጫዋቹ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

ግለቱ ተፋፍሞ በቀጠለዉ ጨዋታ መቻሎች በሽመልስ በቀለ አማካኝነት ከርቀት ድንቅ ሙከራ አድርጎ ግብ ጠባቂዉ በረከት ሲመልስ ፤ በፍቃዱ አለማየሁም አስደናቂ ሙከራን ማድረግ ችሏል። አጋማሹ ተጠናቆ በተሰጠ የጭማሪ ደቂቃ ላይ ግን ቡናማዎቹ የአቻነት ግብ አግኝተዋል። በዚህም ከኋላ ክፍል ዋሳዋ ጆፍሬ ያሻማዉ ኳሷ ግብ ጠባቂዉ መቆጣጠር ሳይችለዉ አምልጦት ያገኘዉ አማኑኤል አድማሱ ኳሷን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል።

ከዕረፍት መልስ ሁለቱም ክለቦች ምንም እንኳን በሙከራ ረገድ የተቀዛቀዘ ሁለተኛ አጋማሽ ያሳልፉ እንጅ ነገር ግን ቡናማዎቹ በይበልጥ ኳስን መስርተዉ ከራሳቸዉ የሜዳ ክፍል ለመዉጣት በመሞከር እና መሐል ሜዳዉን በመቆጣጠር ጫናዎችን ለመፍጠር እና ዕድሎችን ፈጥረዉ ጨዋታዉን ለመምራት ሲጥሩ ፤ በተቃራኒው መቻሎች ደግሞ ወደ መስመር ካደሉ ኳሶች ዕድሎችን ለመፍጠር እና ግብችን አስቆጥረዉ በጨዋታው ላይ መሪ ለመሆን ሲጥሩ ተስተውሏል። በዚህ ሂደት የቀጠለዉ ጨዋታ በቀሪ ደቂቃዎች ላይ ግብ ሳይቆጠርበት አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በባሲሩ ዑመር የመጨረሻ ደቂቃ ግብ ሲዳማ ቡናን ማሸነፍ ችለዋል።

በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ መሪነት ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በጀመረዉ ተጠባቂ ጨዋታ የሊጉ መሪ ሆነዉ ጨዋታዉን የጀመሩት ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የጨዋታዉን እንቅስቃሴ በመቆጣጠር በአንድ ሁለት ቅብብል ተጋጣሚ ቡድን ሳጥን ውስጥ ከደረሱ በኋላ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ በዚህም በመጀመሪያው አጋማሽ ከነበሩ ሙከራዎች መካከል በግራ መስመር በኩል አዲስ ግደይ ከደስታ ዮሐንስ የተቀበለዉን ኳስ የግል ክህሎቱን ተጠቅሞ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም መክብብ ደገፉ ግን ኳሷን ግብ ከመሆን ታድጓል።

የተጋጣሚያቸው የጨዋታ ሂደት ላይ የተመረኮዘ የጨዋታ መንገድን ይዘዉ ወደ ሜዳ የገቡት ሲዳማ ቡናዎች በአብዝሀኛዉ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በመስመር በኩል የነበሩ ጫናዎችን በመዝጋት እና አልፎ አልፎ በሚገኙ የመልሶ ማጥቃት ዕድሎችም ግብ ለማስቆጠር ሲጥሩ ተስተውሎ አጋማሹ ያለ ግብ ተጠናቋል። በሁለተኛዉ አጋማሽ ሁለቱም ክለቦች በርከት ያሉ የማጥቃት ባህሪ ያላቸዉን ተጫዋቾች ቀይረዉ በማስገባት ጨዋታዉን ለመቆጣጠር ሞክረዋል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ 76ተኛዉ ደቂቃ ላይ የሲዳማ ቡናማዉ አማካኝ ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ባሲሩ ዑመር ላይ በሰራዉ ጥፋት በሁለተኛ ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።

በ81ኛዉ ደቂቃ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተከላካዮች የሰሩትን ስህተት ተከትሎ የተገኘዉን ኳስ በቅርበት የነበረዉ አጥቂዉ ኪፕሩል በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ፍሬዉ ጌታሁን ግን በግሩም ብቃት ኳሷን መልሷል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ በ86ተኛዉ ደቂቃ ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የመሪነት ግብ አግኝተዋል። በዚህም በግራ መስመር በኩል ኤፍሬም ወደ ዉስጥ ያቀበለዉን ኳስ አማካዩ ባሲሩ ዑመር ወደ ግብነት ቀይሮ በመጨረሻው ደቂቃ ክለቡ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታዉን 1ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ድሬዳዋ ከተማ እና ወላይታ ዲቻ የድሬዳዋ ቆይታቸዉን በድል ደምድመዋል !!
Next Article የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የተጨዋቾች የዝውውር ድርድር እንዲቆም አዘዘ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

​የቶታል አፍሪካ  ቻምፒዮንስ ሊግ እና የቶታል አፍሪካ  ኮንፌድሬሽን ዋንጫ ድልድል ዛሬ አመሻሽ ላይ ይፋ ሆኗል!!!

hatricksport team By hatricksport team 9 years ago
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋንጫ | ኢትዮጵያ ቡና ከ አዳማ ከተማ
“እንደ አንድ የጊዮርጊስ ደጋፊ ይህ ያለ ውጤት ጉዞው ዘንድሮ ቢያበቃ ደስ ይለኛል ” አሰልጣኝ ሚሎቲን ሰሬዶዬቪች ሚቾ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ቀጣዩ ዙር መቀላቀል ሳይችል ቀርቷል።
የጨዋታ ዘገባ | አዲስ አበባ ከተማ ዛሬም እየመራ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?