By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ለገጣፎ ለገዳዲ ሲዳማ ቡናን አሸንፏል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ለገጣፎ ለገዳዲሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ለገጣፎ ለገዳዲ ሲዳማ ቡናን አሸንፏል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 5 months ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ29ነኛ ሳምንት ጨዋታ ሶስተኛ ዕለት የመጀመሪያ ጨዋታ መውረዱን ያረጋገጠው ለገጣፎ ለገዳዲ በጥሩ መሻሻል ላይ ይገኝ የነበረዉን ሲዳማ ቡና 3ለ2 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

ከመርሐግብሩ መጀመር አስቀድሞ በርካቶች ለሲዳማ ቡና የማሸነፍ ቅድመ ግምት በሰጡበት ጨዋታ በመጀመሪያዎቹ አስራ አምስት ሀያ ያህል ደቂቃዎች ባልተጠበቀ መልኩ ለገጣፎ ለገዳዲ በጨዋታዉ ተሽለው ሲንቀሳቀሱ በሙከራ ረገድም በ18ተኛዉ ደቂቃ ላይ የፊት መስመር ተጫዋቹ ቴዲ ንጉሱ በከተፈራ አንለይ የተሻገረለትን ኳስ በቀታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም በግብ ዘቡ አዱኛ ፀጋየ አማካኝነት ኳሷ ግብ ከመሆን መክናለች።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ለገጣፎ ለገዳዲ ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም በ21ኛዉ ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተሻማዉን ኳስ ቁመተ መለሎዉ አጥቂ ካርሎስ ዳምጠዉ በግንባሩ በመግጨት ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

በተቃራኒው በጨዋታው ደካማ አጀማመር ያደረጉት ሲዳማዎች በተለይ በመጀመሪያው አጋማሽ በለገጣፎ ብሎጫ ተወስዶባቸዉ ግብ ለማስቆጠርም ሆነ ለግብ የቀረበ ሙከራ ለማድረግ ሲቸገሩ ሲስተዋል በ27ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን በአጋማሹ ተጠቃሽ ሙከራን በአማካዩ አበባየሁ ዮሀንስ አማካኝነት ማድረግ ችለዋል። በዚህም በጥሩ ቅብብል ከመሐል ክፍል የተቀበለዉን ኳስ አማካዩ ከርቀት በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም የግብ ዘቡ ኮፊ ሜንሳህ እንደምንም መልሶበታል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም አጋማሹ ሊጠናቀቅ አራት ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩ በ41ኛዉ ደቂቃ ላይ መሪነታቸዉን ወደ ሁለት ከፍ ማድረግ የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ግብ ጠባቂዉ አዱኛ ፀጋየ የመለሰዉን ኳስ አጥቂዉ አማኑኤል አረቦ በአስደናቂ እይታ ወደ ግብነት በመቀየር የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ማድረግ ችሏል።

ከዕረፍት መልስ በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ቀይረዉ ወደ ሜዳ በማስገባት ወደ ጨዋታው ለመመለስ የሞከሩት ሲዳማዎች በጥሩ የመሐል ሜዳ እንቅስቃሴ በጨዋታዉ አደጋ ለመፍጠር በሚጥሩበት ወቅት በ62ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሶስተኛ ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም የፊት መስመር ተጫዋቹ ሱለይማን ትራኦሬ ለራሱ የመጀመሪያውን ለክለቡ ደግሞ ሶስተኛ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

ገና በጨዋታዉ 60 ያህል ደቂቃዎች ሳይጠበቅ በለገጣፎ ሶስት ጎል ያስተናገዱት ሲዳማዎች ደግሞ በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ተከላካዩ ያኩቡ መሐመድ ከርቀት አክርሮ ወደ ግብ የላካት ኳስ የግብ ጠባቂዉ ኮፊ ሜንሳህ መረብ ላይ አርፋለች።

ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸውን ግብ ማስቆጠር ከቻሉ በኋላ ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት ሲዳማዎች በ79ነኛዉ ደቂቃ ላይ በግራ ተከላካዩ መሐሪ መና አማካኝነት ድንቅ ሙከራ አድርገዉ በድጋሚ ከሰባት ደቂቃዎች በኋላ በ86ተኛዉ ደቂቃ ደግሞ በዚሁ ተጫዋች አማካኝነት ግብ ማስቆጠር ችለዋል።

በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ ጫና ፈጥረዉ ሁለት ጎሎችን ማስቆጠር የቻሉት ሲዳማ ቡናዎች ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ በለገጣፎ ለገዳዲ 3ለ2 በሆነ ዉጤት የተሸነፉ ሲሆን በጨዋታዉ መገባደጃ ወቅትም የለገጣፎዉ አጥቂ ሱለይማን ግብ ጠባቂዉ አዱኛ ፀጋየ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ደረጃቸዉን ማሻሻል የቻሉበት ዉጤት አስመዝግበዋል !!
Next Article የጨዋታ ዘገባ |ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ጨዋታ እየቀረዉ የሊጉ ሻምፒዮን መሆን የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ኢንተርሚዲየሪዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

“የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለፊፋ የመክሰስ ሃሳባችንን ትተነዋል” አቶ በረከት ደረጀ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኢንተርሚዲየሪዎች ማኅበር ም/ፕሬዚዳንት

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ 7ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ጨዋታዎች ውጤት
የጨዋታ ዘገባ | ክትፎዎቹ አሸናፊነታቸውን አስቀጥለዋል
የአሰልጣኞች አስተያየት | ቅዱስ ጊዮርጊስ 0-1 ወልቂጤ ከተማ
የጨዋታ ዘገባ | የጦና ንቦቹ እና አዳማ ከተማ ያደረጉት የዕለቱ የመጀመሪያ መርሐግብር በአቻ ዉጤት ተገባዷል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?