By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ደረጃቸዉን ማሻሻል የቻሉበት ዉጤት አስመዝግበዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችኢትዮ-ኤሌክትሪክየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግፋሲል ከነማ

የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ደረጃቸዉን ማሻሻል የቻሉበት ዉጤት አስመዝግበዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሀያ ዘጠነኛ ሳምንት ሁለተኛ ዕለት ሁለተኛ ጨዋታ የአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ቡድን ፋሲል ከነማ አስቀድሞ መዉረዱን ያረጋገጠዉን ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በርከት ያሉ የተጫዋቾች ለዉጥ አድርገዉ ወደ ሜዳ በገቡት ፋሲል ከነማዎች የረጃጅም ኳስ እና የቆሙ ኳሶች ማጥቃት እንዲሁም በኢትዮ ኤሌትሪኮች የመሐል ሜዳ የተሻለ እንቅስቃሴ በጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ቀዳሚ ተጠቃሽ ሙከራ በማድረግ ረገድ አፄዎቹ ቀዳሚ ነበሩ ፤ በዚህም በጨዋታው መባቻ 12ተኛ ደቂቃ ላይ አማካዩ ይሁን እንዳሻዉ ከአጥቂዉ ኦሴ ማውሊ የተቀበለዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች።

ከዚች ሙከራ በኋላ ምንም እንኳን በሜዳዉ የመሐል ክፍል ኤሌትሪኮች የተሻለ መንቀሳቀስ ቢችሉም ነገር ግን በመጀመሪያዉ አጋማሽ ተጠቃሽ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረዉ በተቃራኒው የመጀመሪያው አጋማሽ ሊገባደድ አምስት ያህል ደቂቃዎች በቀሩበት ወቅት ግብ አስተናግደዋል። በዚህም በ40ኛዉ ደቂቃ ላይ አጥቂዉ ኦሴ ማዉሊ ከአማካዩ አቤል እያዩ የተቀበለዉን ኳስ ለመስመር ተጫዋቹ አለም ብርሀን ይግዛው አቀብሎት ተጫዋቹ  የግል ቅልጥፍናዉን ተጠቅሞ ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ ተሻሽለዉ ወደ ሜዳ የተመለሱ የሚመስሉት አፄዎቹ በ50ኛዉ ደቂቃ ላይ መሪነታቸውን ወደ ሁለት ከፍ ማድረግ የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ከቀኝ የፋሲል ከነማ ማጥቃት በኩል የመስመር ተጫዋቹ ዱላ ሙላቱ በአስገራሚ ብቃት ለአጥቂዉ ለኦሴ ኦሴ ያቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ በቶሎ ወደ ግብነት በመቀየር የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ከፍ ማድረግ ችሏል።

ሁለተኛ ግብ ካስቆጠሩ በኋላ የማጥቃት ሀይላቸዉን አጠንክረዉ የቀጠሉት አፄዎቹ በአማካዩ ይሁን እንዳሻዉ እንዲሁም አጥቂዉ ኦሴ ማውሊ ከርቀት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን በማድረግ ለግብ ዘቡ ካክፖሸሪፍ ፈተና ሲሆኑበት ተስተውሏል። በተቃራኒው ሁለት ያህል ግብ ካስተናገዱ በኋላ በመጨረሻዎቹ አስር ያህል ደቂቃዎች ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቻሉት ኤሌትሪኮች በ86ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በተጠቀሰዉ ደቂቃ ከመዓዘን ምት የተሻማዉን ኳስ አብዱራህማን ሙባረክ በግንባሩ በመግጨት ግብ በማስቆጠር ክለቡን ወደ ጨዋታው መመለስ ችሏል።

ኢትዮ ኤሌትሪኮች ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን ግብ ማስቆጠር ከቻሉ በኋላ አቻ ለመሆን ከፍተኛ ጥረት ማድረግ የቀጠሉት ኤሌክትሪኮች በአብዱራህማን ሙባረክ እና ስንታየሁ ሞለጬ በመሳሰሉ ተጫዋቾች ተደጋጋሚ ሙከራ ማድረግ ቢችሉም ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ በጨዋታውም በአፄዎቹ 2ለ1 በሆነ ዉጤት ተሸንፈዋል።

ዉጤቱን ተከትሎም በጨዋታው ድል የቀናዉ ፋሲል ከነማ በ42 ነጥብ ወደ  አራተኛ ደረጃ ከፍ ሲል በተቃራኒው ሽንፈት ያስተናገደዉ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ደግሞ በ12 ነጥብ አስራ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድኅንን በሶስት ግብ ልዩነት አሸንፏል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ለገጣፎ ለገዳዲ ሲዳማ ቡናን አሸንፏል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ወላይታ ድቻአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | የያሬድ ዳዊት ብቸኛ ግብ ለጦና ንቦቹ ሶስት ነጥብ አስገኝታለች

hatricksport team By hatricksport team 4 years ago
“ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ተገኝቶ ያልተካሄደ የውል ፊርማ በቢቢሲ በሲኤንኤን በአልጀዚራ ቢታይም ትርጉም የለውም”አቶ ገዛኸኝወልዴ /ኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዋና ስራ አስኪያጅ/
12ኛ የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ ቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/
ፌዴሬሽኑ የ2009 ዓ.ም ውድድሮችን በልዩ የሽልማት ስነስርዓት ለማከናወን እየሰራ መሆኑን ገለፀ ፤የዘንድሮ ሻምፒዮን ለሚሆነው ቡድን የሚሰጠው የገንዘብ መጠን ከፍ ለማድረግም ታቅዷል
ወጣቱ አጥቂ ጉዳት አጋጥሞታል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?