By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድኅንን በሶስት ግብ ልዩነት አሸንፏል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባኢትዮጵያ መድህን

የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድኅንን በሶስት ግብ ልዩነት አሸንፏል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን መርሐግብሮች በዛሬው ዕለትም ቀጥለው ሲደረጉ በቀዳሚው ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድኅንን 3 – 0 አሸንፏል ።

በጨዋታው በአዳማ ከተማ በኩል በ28ኛው ሳምንት ከሀድያ ሆሳዕና አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ ብቻ በማድረግ አድናን ረሻድን በአሜ መሐመድ ተክተው ጨዋታውን ጀምረዋል ። በኢትዮጵያ መድኅን በኩል በሳምንቱ ኢትዮጵያ ቡና በረቱበት ጨዋታ ከነበረው ምርጥ 11 ሶስት ለውጦች በማድረግ ሀቢብ መሐመድ ፣ ያሬድ ካሳዬ እና እዮብ ገብረማርያምን በተካልኝ ደጀኔ ፣ ፀጋሰው ድማሙ እና ሀቢብ ከማል ምትክ አሰልፈዋል ።

በጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር የተጀመረው ጨዋታ በሁለቱም በኩል ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ጥረቶችን በማድረግ የጀመሩት ነበር ። በአንፃራዊነት በኳስ ቁጥጥሩ የተሻሉ የነበሩት ኢትዮጵያ መድኅኖች የአዳማ ከተማን የኋላ መስመር አልፈው የግብ ዕድል ለመፍጠር ደቂቃዎች ወስደውባቸው ነበር ።

- ማሰታውቂያ -

በአዳማ ከተማም ሆነ በኢትዮጵያ መድኅን በኩል የነበረው የጨዋታ እንቅስቃሴም በግብ ሙከራዎች ሳይታጀብ እስከ 17ኛው ደቂቃ ተጉዞ ነበር ።

በ17ኛው ደቂቃ ላይ የመጀመሪያ ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራ የተደረገ ሲሆን ሳይመን ፒተር የአዳማ ከተማው ግብ ጠባቂ ሰይድ ሀብታሙ ከግብ ክልሉ መውጣቱን ተመልክቶ ወደ ግብ የመታውን ግብ ጠባቂው ለጥቂት ግብ ከመሆን አድኖታል ።

በአዳማ ከተማ በኩል ቀዳሚው ጠንካራ የግብ ሙከራ ከተጋጣሚያቸው የግብ ሙከራ አራት ደቂቃዎች በኋላ የተደረገ ነበር ። አጥቂው ዳዋ ሆጤሳ በኢትዮጵያ መድኅን ሳጥን ውስጥ ወደ ቀኝ ባደላ ቦታ የደረሰውን ኳስ አክርሮ ወደ ግብ ቢመታም በግብ ጠባቂው አቡበከር ኑራ ተመልሶ ወጥቷል ።

በ28ኛው ደቂቃ ላይ በኢትዮጵያ መድኅን በኩል ከግራ መስመር አቅጣጫ የተሻገረውን ኳስ ቴዎድሮስ በቀለ በግንባር በመግጨት ለባሲሩ ኡመር ቢያቀበልም ከባሲሩ ቀድሞ ሰይድ ሀብታሙ ኳሱን ተቆጣጥሮታል ።

በፈጣን እንቅስቃሴዎች የኢትዮጵያ መድኅንን የተከላካይ መስመር ለመፈተን የቻሉት አዳማ ከተማዎች በ32ኛው ደቂቃ ላይ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል ።

መስዑድ መሐመድ ከማዕዘን ከሳጥኑ ውጪ ለነበረው ደስታ ዮሐንስ ያቀበለውን ኳስ የግራ መስመር ተከላካዩ ደስታ ከርቀት አክርሮ በመምታት አስደናቂ ግብ ከመረብ አሳርፏል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለጊዜም በአዳማ ከተማ የ1 – 0 መሪነት ተጠናቀቀ ።

በሁለተኛው አጋማሽ ኢትዮጵያ መድኅኖች ወደ አቻነት ለመመለስ ጥረቶችን በማድረግ የጀመሩት ቢሆንም ወደ ግብ ክልል ደርሶ ጠንካራ የግብ ዕድሎች ከመፍጠሩ አንፃር አዳማ ከተማዎች የተሻሉ ነበሩ ።

በአጋማሹ ቀዳሚ የግብ ሙከራም በ57ኛው ደቂቃ ላይ ዮሴፍ ታረቀኝ ከቀኝ መስመር የተሻገረለትን ኳስ በግንባር ገጭቶ ለማስቆጠር ያደረገው ሙከራ ኢላማውን ሳይጠብቅ ቀርቷል ።

ከስድስት ደቂቃዎች በኋላም ቢንያም አይተን ከሳጥን ውጪ ያደረገው ሙከራ በአቡበከር ኑራ ተይዟል ። አዳማ ከተማዎች በፈጣን እንቅስቃሴዎች የተሻለ የግብ ዕድል መፍጠር ችለው በቀጠለቡት የሁለተኛው አጋማሽ ኢትዮጵያ መድኅኖች ወደ ተጋጣሚያቸው የግብ ክልል ለመድረስ ተቸግረው ቆይተዋል ።

ጨዋታው 78ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስም የቢንያም አይተን ድንቅ ግብ የአዳማ ከተማን መሪነት ወደ 2 – 0 ከፍ አድርጓል ። ቢንያም አይተን ከሀብታሙ ሸዋለም ስህተት ያገኘውን ኳስ አንድ ለአንድ ከተገናኘው አብዱልከሪም መሐመድ ጋር ተፋልሞ ለአቡበከር ኑራ ምንም ዕድል ሳይሰጥ ግሩም ግብ አስቆጥሯል ።

ከስምንት ደቂቃዎች በኋላም አዳማ ከተማዎች መሪነታቸውን ወደ 3 – 0 ያደረሱበትን ግብ በዳዋ ሆጤሳ አማካኝነት አስቆጥረዋል ። ኤልያስ ለገሰ ከቀኝ አቅጣጫ ይዞ ገብቶ ለዳዋ ሆጤሳ የቀነሰለትን ኳስ አጥቂው ከመረብ አሳርፎታል ።

በመጨረሻም በአዳማ ከተማ የ3 – 0 አሸናፊነት ጨዋታው ፍፃሜውን አግኝቷል ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ለ2016 ኢትዮ ኤሌክትሪክን ተረከበ
Next Article የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ደረጃቸዉን ማሻሻል የቻሉበት ዉጤት አስመዝግበዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

እንደሁሌው አሁንም ሀትሪክ በቀኗና በሰአቷ በመገኘት ቃሏን እንደጠበቀች ነው… ነገ ጠዋት ሀትሪክ እጅዎ ስትገባ……

hatricksport team By hatricksport team 5 years ago
ድሬድዋ ከተማ ተጫዋች ማስፈረሙን ቀጥሏል
የኢትዮጵያ ወንድ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የማበረታቻ ሽልማት እና እውቅና ሊበረከትለት ነው ፡፡
Des arbitres ethiopiens arbitreront le derby tunisien
ጀማል ጣሰው ለዋሊያዎቹ ተጠርቷል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?