By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ |ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ጨዋታ እየቀረዉ የሊጉ ሻምፒዮን መሆን የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ |ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ጨዋታ እየቀረዉ የሊጉ ሻምፒዮን መሆን የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

 

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሀያ ዘጠነኛ ሳምንት የመጨረሻ ዕለት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀድያ ሆሳዕናን በሆነ ዉጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል።

የውድድር አመቱን በሻምፒዮንነት ለማገባደድ ከጨዋታዉ አንድ ነጥብ ብቻ ይፈልግ የነበረዉ የአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ ቡድን ቅዱስ ጊዮርጊስ የሜዳ ላይ ብልጫ ወስዶ በጀመረበት የቀን ዘጠኝ ሰዓቱ መርሐግብር ላይ ፈረሰኞቹ የተሻለ ብልጫ ወስደዉ ሲንቀሳቀሱ ሲስተዋል ፤ በተቃራኒው ነብሮቹ ሀድያ ሆሳዕናዎች ደግሞ በይበልጥ ጥንቃቄ ላይ ባመዘነ የጨዋታ መንገድ አልፎ አልፎ በሚገኙ ረጃጅም ኳሶች በጨዋታዉ አደጋ ለመፍጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።

- ማሰታውቂያ -

በዚህ ሂደት በጀመረዉ ጨዋታም በ10ኛዉ ደቂቃ ላይ የመጀመሪያዉ ተጠቃሽ ሙከራ ተደርጎበታል ፤ በዚህም ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመሐል ክፍል ወደ ፊት የተሻገረዉን ኳስ የሀድያ ተከላካዮች ወደ ዉጭ ካወጡት በኋላ ሄኖክ አዱኛ ያሻማዉን የመዓዘን ኳስ ናትናኤል ዘለቀ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ኢላማዋን ሳትጠብቅ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

12ተኛዉ ደቂቃ ደግሞ ተከላካዩ ምኞት ደበበ በቀጥታ በረጅሙ ለኢስማኤል ኦሮ አጎሮ የጣለዉን ኳስ አጥቂዉ ከተከላካዮች ጋር ታግሎ እንደምንም ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ፔፔ ሰይዶ በፍጥነት ወጥቶ ኳሷን አውጥቷታል።

በጨዋታዉ 20ኛ ደቂቃ ላይ ግን ፈረሰኞቹ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም አማካዩ ናትናኤል ዘለቀ ለመስመር ተጫዋቹ ቸርነት ጉግሳ ያቀበለዉን ኳስ ተጫዋቹ ከሳጥኑ ጠርዝ በቀጥታ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

ከግቧ መቆጠር ከደቂቃዎች በኋላ ደግሞ በ24 ተኛዉ ደቂቃ ላይ የግራ መስመር ተከላካዩ ረመዳን የሱፍ ሳጥን ዉስጥ ያቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ አጎሮ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ የግብ ዘቡ ፔፔ ሰይዶ ኳሷን ወደ ዉጭ አዉጥቷታል።

በተቃራኒው በመጀመሪያው አጋማሽ ተጠቃሽ የግብ ሙከራ ለማድረግ የተቸገሩ የሚመስሉት ሀድያዎች በግልፅ በተደጋጋሚ ረጃጅም ኳሶችን ወደ ፊት መስመር በመጣል በአጥቂዎቹ ፀጋየ ብርሐኑ እና ባየ ገዛኸኝ አማካኝነት አደጋ ለመፍጠር ሲጥሩ የነበረ ሲሆን ነገር ግን በአጋማሹ ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን ግብም ሆነ አደገኛ ተጠቃሽ ሙከራ ሳያደርጉ ሁለቱም ክለቦች ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ ይበልጥኑ ተሻሽለዉ የተመለሱት ጊዮርጊሶች ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በ49ነኛዉ ደቂቃ ላይ ከቀኝ ማጥቃት በኩል ሄኖክ አዱኛ ያሻማዉን የቅጣት ምት ኳስ ረመዳን ከተቆጣጠረ በኋላ ወደ ሳጥን ሲያሻማ ልማደኛዉ አጥቂ ኦሮ አጎሮ በግንባሩ በመግጨት ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ማድረግ ችሏል።

በ59ነኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ በአብዝሀኛዉ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ አደጋ ለመፍጠር የቸቸገሩት ነብሮቹ ሙከራ ማዶረግ ችለዋል ፤ በዚህም የመስመር ተጫዋቹ ተመስገን ብርሀኑ ከአጥቂዉ ባየ ገዛኸኝ የተቀበለዉን ኳስ ከሳጥን ውጭ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት የግቡን ቋሚ ታካ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

የጨዋታዉ ደቂቃ እየገፋ በመጣ ቁጥር ጫናቸዉን አበርትተዉ የቀጠሉት ፈረሰኞቹ በአጥቂዉ ኢስማኤል ኦሮ አጎሮ ፣ አቤል ያለዉ እና ቸርነት ጉግሳን በመሳሰሉ ተጫዋች ለግብ የቀረቡ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ እና ግብም ሳይስተናገድባቸዉ ጨዋታዉን 2ለ0 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ አንድ ጨዋታ እየቀራቸዉ የ2015 አመት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮን መሆን የቻሉበትን ዉጤት ማስመዝገብ ችለዋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ለገጣፎ ለገዳዲ ሲዳማ ቡናን አሸንፏል !!
Next Article የጨዋታ ዘገባ | የዓብስራ ተስፋዬ አስደናቂ ግብ የጣና ሞገዶቹን አሸናፊ አድርጓል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

ሀትሪክ በነገው እትሟ ባለቀለሟ እና ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገም ከእናንተ ውድ አንባቢዎቿ ጋር በዘገባዋ ለመገናኘት ስራዋን አጠናቃለች፡፡

Mussie Girmay By Mussie Girmay 7 years ago
የሀገር አቀፍ ክልል ክለቦች  ሻምፒዮና ጉለሌ ክ/ከተማ ከሰንዳፋ በኬ ለዋንጫ ደረሰዋል
የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰቦች  የሁለተኛው ዙር አመታዊ ሩጫ በተመለከተ በሂልተን ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሠጠ፡፡
ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ የቀድሞ አሰልጣኙን ለመቅጠር ከጫፍ ደርሷል
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሯጮች የመለያ ቁጥር   ካለጠፉ ወደ መሮጫ ቦታ አይገቡም ተባለ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?