By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ከሁለት አመታት በኋላ አርባምንጭ ከተማ ዳግም ወደ ከፍተኛ ሊጉ ተመልሷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችሀዋሳ ከተማአርባምንጭ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ከሁለት አመታት በኋላ አርባምንጭ ከተማ ዳግም ወደ ከፍተኛ ሊጉ ተመልሷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

 

ወሳኝ በነበረዉ እና ሶስተኛዉን የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወራጅ ቡድን የሚለየዉ አንደኛዉ መርሐግብር በነበረዉ የቀን ዘጠኝ ሰዓት የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም የ30ኛ ሳምንት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ከሀዋሳ ከተማ 1ለ1 በሆነ ዉጤት አቻ  መርሐግብራቸዉን አጠናቀዋል።

በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ መሪነት የተጀመረዉ ወሳኙ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም በጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር ሲጀምር ገና በመባቸዉ በ2ተኛዉ ደቂቃ ላይም ተመስገን ደረሰ ያቀበለዉን ኳስ በላይ ገዛኸኝ ወደ ግብ ሞክሮ የበነበረ ቢሆንም የግብ ዘቡ አልዓዛር መልሶበታል።

- ማሰታውቂያ -

ከጨዋታዉ መጀመሪያ አንስቶ በሙከራ ረገድ የተሻሉ የነበሩት እና የጨዋታዉን ዉጤት አብዝተዉ ይፈልጉት የነበሩት አዞዎቹ በ13ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም የመስመር ተጫዋቹ ተመስገን ያቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ አህመድ ሁሴን በድንቅ ብቃት ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

በጨዋታዉ እንቅስቃሴም ሆነ በሙከራ ረገድ ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሀይቆቹ ከኋላ ወደ አጥቂዎቹ በሚጣሉ ረጃጅም ኳሶች አልፎ አልፎ ግብ ለማስቆጠር ሲያደርጉት የነበረዉ ጥረት ተሳክቶላቸዉ በ23ተኛዉ ደቂቃ ላይ አቻ መሆን ችለዋል ፤ በዚህም አጥቂዉ ሙጅብ ቃሲም ያሻገረለትን ኳስ እዮብ አለማየሁ ወደ ግብ በመቀየር ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም አርባምጭ ከተማ በመስመር ተጫዋቾቹ ተመስገን ደረሰ ፣ አህመድ እና በላይ ገዛኸኝ በመሳሰሉ ተጫዋቾች ጥሩ ጥሩ ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም በመጀመሪያው አጋማሽ ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዋል። በተመሳሳይ ሀዋሳ ከተማም በተከታታይ በአሊ ሱለይማን እና ሙጅብ አማካኝነት ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም ሁለቱም ክለቦች ተጨማሪ ግብ ሳያስቆጥሩ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

 

ከዕረፍት መልስ በተመሳሳይ የጨዋታ መንገድ በቀጠሉት በሁለቱ ክለቦች ጨዋታም በ51ኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ አቡበከር ሻሚል ከመላኩ ኤልያስ የተቀበለዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ በግቡ አናት ላይ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

ከደቂቃዎች በኋላ በ54ተኛዉ ደቂቃ ላይ በድጋሚ አጥቂዉ አህመድ ሁሴን ከመሐል ሜዳ እየገፋ ሳጥን ዉስጥ ከገባ በኋላ አጥቂዉ ኳሷን ለመላኩ ሲያቀብለዉ እርሱ ደግሞ ለተመስገን ደረሰ በጥሩ አመቻችቶለት የነበረ ቢሆንም ተጫዋቹ በቀጥታ ኳሷን ወደ ግብ ሲሞክር ግብ ጠባቂዉ አልዓዛር ማርቆስ እንደምንም ኳሷን መልሷታል።

በ74ተኛዉ ደቂቃ አጥቂዉ አህመድ ሁሴን ተከላካዮችን አታሎ ሳጥን ዉስጥ ከደረሰ በኋላ ወደ ግብ የሞከረዉን ኳስ በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ የግብ ዘቡ አልዓዛር ሲመልሰዉ ኳሷ ሌላኛዉን አጥቂ ተመስገን ደረሰ ጨርፋ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች። የጨዋታው ደቂቃ እየገፋ በመጣ ቁጥር አዞዎቹ ጫናቸዉን አበርትተዉ ሲቀጥሉ ፤ በተቃራኒው ሀይቆቹ በፊት መስመር ተጫዋቾቻቸው ኢላማቸዉን ያልጠበቁ ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም ሁለቱም ክለቦች የማሸነፊያ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ መደበኛዉ 90 ደቂቃ 1ለ1 በሆነ አቻ ዉጤት ተገባዷል። ዉጤቱን ተከትሎም አርባምንጭ ከተማ ከሊጉ የወረደ ሶስተኛዉ ክለብ ሆኗል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | አዞዎቹ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርደዋል
Next Article “ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወሰዳቸው አብዛኛዎቹ ዋንጫዎች ውስጥ በተጨዋችነትም ይሁን በአሰልጣኝነት ስላለሁበት ኩራት ይሰማኛል” አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣUncategorized

የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ጉዳይ ዕልባት አላገኘም፤ቴክኒክና ልማት ምርጫውን ቢያጠናቅቅም ፌዴሬሽኑ እስከአሁን ምርጫውን አላፀደቀውም

Yishak belay By Yishak belay 9 years ago
መረጃዋን ስታቀርብልዎ በሙሉ ክብር ነው …. ሀትሪክ እንዲህ ናት
ቅድመ ዳሰሳ | ወላይታ ድቻ ከፋሲል ከነማ
“ከውጤትም ከጥሩ እንቅስቃሴም አንፃር ምርጥ ጊዜን እያሳለፍን ነው”አቤል ከበደ /ኢትዮጵያ ቡና/
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ እና ሰበታ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?