By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ደመወዙ ይፋ ባልተደረገበት መድረክ ፋሲል ከነማ       አሰልጣኝ ውበቱ አባተን መሾሙን አስታወቀ…
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የዝውውር ዜናዎችዜናዎችቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግፋሲል ከነማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ደመወዙ ይፋ ባልተደረገበት መድረክ ፋሲል ከነማ       አሰልጣኝ ውበቱ አባተን መሾሙን አስታወቀ…

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
Share
SHARE

“በሊጉ አሁን ከሚከፈል ደመወዝ
ያልተጋነነ ክፍያ እንከፍላለን”
አቶ ባዩ አቡሃይ
/የክለቡ ፕሬዝዳንት/

“በፕሪሚየር ሊጉ የተሻሉ ከሚባሉ አሰልጣኞች
ያላነሰ ደመወዝ ይከፈለኛል”
አሰልጣኙ ውበቱ አባተ

“ከሚዲያ ጋር መልካም ግንኙነት አለን ነገር ግን የማያተርፍ ዜና ይፋ ማድረግ  አይጠበቅብንም…”
አቶ አቢዮት ብርሃኑ
/ዋና ስራ አስኪያጅ/

” እንኳን 20 አዳዲስ ተጨዋች ማስፈረም የቤት እቃ  ከቦታ ቦታ ማመላለስ ይከብዳል”
አሰልጣኝ ውበቱ  አባተ

- ማሰታውቂያ -

“በፋሲል ከነማ ያየሁት የደጋፊ ስሜትና የአመራሩ ቁርጠኝነት ፣ የክለቡ አመራሮች ያሳዩኝ ክብርና በክለቡ ረዘም ያለ ጊዜ የምሰራበት መንገድ መመቻቸቱ ፋሲል ከነማን እንድመርጥ አድርጎኛል” ሲሉ አዲሱ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ  ውበቱ አባተ ተናገሩ።

የሀትሪክ ድረገጽ  ከታማኝ ምንጭ ባገኘችው መረጃ አሰልጣኙ  ከወራት በፊት ለቀጣዩ ሶስት አመት ከፋሲል ከነማ ጋር ለመስራት መስማማታቸውን መዘገቡ የሚታወስ ሲሆን  ክለቡና አሰልጣኙም ዛሬ በጁፒተር ሆቴል በሰጡት ይፋዊ  መግለጫ  ይፋ  አድርገውታል ።

“ፋሲል ከነማ የጎንደር አርማ ነው ክለባችን  የኢትዮዽያ እግርኳስ  ክስተት እንደሆነም ይታወቃል ከ2009 ጀምሮ በሀገሪቱ እግርኳስ ትልቅ አሻራ አምጥቷል ባለፉት አመታት በተከሰተው መጠነኛ  የውጤት  ማጣት በመገንዘብና ሂደቶችን ከመሰረቱ  በመገምገም የ5 አመት ስትራቴጂ በማዘጋጀት  አሰልጣኝ ውበቱ አባተን ሾመናል” ያሉት የጎንደር ከተማ ከንቲባና የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ ባዩ አቡሃይ ” አሰልጣኝ ውበቱ በቀጣዪቹ 3 አመታት  በገባው ውል  በ2016  ቡድናችንን ዋና ተፎካካሪ እንዲያደርጉ  በ2017 ደግሞ ዋንጫ እንዲያመጡ ተስማምተናል። ከዚህ ውጪ  ክለባችንን  በምስራቅ አፍሪካ የሚታወቅ  ክለብ እንዲሆን ማስቻል፣በዚህ ታሪካዊና በህዝብ ልብ ውስጥ የታተመ ክለብ   የእግርኳሳችን  ስጋት የሆነው የስነምግባር ጥሰትን  አስወግዶ ተተኪ ታዳጊ እንዲያፈራ ተስማምተናል” ሲሉ አስረድተዋል።

የአራት ወር ደመወዝ ስላለመክፈላቸው የተጠየቁት አመራሮቹ  “ፋሲል  ከነማ ብሄራዊ ሊግም እያለ በደመወዝ አይታማም  በአመራር  ደረጃ  በነበረ ልውውጥ  የነበረ ክፍተት አለ አሁን ተስተካክሏል ክፍተቱም ታርሟል” ሲሉ መልሰዋል። ለዝውውር 100 ሚሊዮን ብር መድባችሁ በርካታ ተጨዋቾች እንድታስፈርሙላቸው አሰልጣኙ ጠይቀዋል ለሚለው ጥያቄ  በተሰጠ ምላሽ “አሰልጣኙን ስንቀጥር መጠነኛ ተጨዋቾችን ጨምሮ  ባሉት ተጨዋቾች ላይ ጠንካራ ቡድን  እንዲገነባ እንጂ  ዝም ብሎ የሚወጣ ብር የለም ክለባችንኮ  በጎ አድራጊ ተቋም  አይደለም እንደ አሰራር አሰልጣኙ ይጠቁማል እንጂ  የዝውውር ኮሚቴ ስላለ ገንዘቡ ላይ  አይገባም” ሲሉ መልሰዋል።  አሰልጣኝ ውበቱም በጉዳዩ ዙሪያ  በሰጡት  ምላሽ ” እንኳን 20 አዳዲስ ተጨዋች ማስፈረም የቤት እቃ  ከቦታ ቦታ ማመላለስ ይከብዳል” ሲሉ መረጃውን አስተባብለዋል።

አሰልጣኝ ውበቱ በበኩላቸው “በየቀኑ ከተጨዋችና ከሚዲያ ጋር መገናኘቱ ይናፍቃል  ዲ ኤስ ቲቪ ሲጀመር አንዱ የሊጉ አካል ባልሆንም ለብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋች  ከዚያ እመርጥ ስለነበር ውድድሮችን  መከታተሌ አልቀረም… ከእቅድ አንጻር በግሌ የማቅደው እቅድ የለም… ክለቡ ያቀደው እቅድ ነው የኔ እቅድ…በቀጣይ ከምንጨምራቸው  አንዳንድ ባለሙያዎች ውጪ  ካሉት አሰልጣኞች ጋር እቀጥላለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።

የአሰልጣኝ ውበቱ ዝውውር  ሲነገር ለምን ቶሎ አስተባበላችሁ የተባሉት  ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ አቢዮት ብርሃኑ በበኩላቸው  ” በወቅቱ የአሰልጣኝ ቦታው በሌላ አሰልጣኝ ተይዞ ነበር  ፌዴሬሽኑም  እንደማይቀበለን እናውቅ ነበር  አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ  ከነበረብን ችግር አውጥቶ ከፍ ያለ ደረጃ ይዘን እንድንጨርስ አስችሏል ይሄም መከበር ነበረበት ለዚህ ነው ያስተባበልነው” ሲሉ ተናግረዋል።

ከሚዲያ ያላችሁ ግንኙነት  ጥሩ  አይመስልም  ይሄስ ለምን የሆነ  ይመስላችኋል..? ለሚለው ጥያቄ ዋና ስራ አስኪያጁ በሰጡት ምላሽ ” እኛ ጥሩ ግንኙነት እንዳለን ነው የምናምነው… በርግጥ ምስጢር መጠበቅ ባለብን ጉዳይ  ላይ እንጠብቃለን..ከአሰልጣኞችና ተጨዋቾች ጋር  ባለን ግንኙነት  ነገሮችን ላለማጦዝና ሚዲያ ላይ ቶሎ ወጥተን ላለመናቆር እንጥራለን  እንደ አጠቃላይ ግን  ከሚዲያ ጋር መልካም ግንኙነት አለን ነገር ግን የማያተርፍ ዜና ይፋ ማድረግ  አይጠበቅብንም…” ሲሉ  መልሰዋል።

በሶስት አመት ውል መሰረት የአሰልጣኙ ደመወዝ  ስንት ነው ..? ተብለው ከሚዲያው ለቀረበ ተደጋጋሚ ጥያቄ አሰልጣኙና አመራሮቹ ቀጥተኛ ምላሽ ያልሰጡ ሲሆን  አሰልጣኙ ውበቱ አባተ “በፕሪሚየር ሊጉ የተሻሉ ከሚባሉ አሰልጣኞች ያላነሰ ደመወዝ ይከፈለኛል” ሲሉ  ፕሬዝዳንቱ በበኩላቸው “በሊጉ አሁን ከሚከፈል ደመወዝ  ያልተጋነነ ክፍያ እንከፍላለን” ሲሉ ተዘዋዋሪ ምላሽ ሰጥተዋል።

ያም ሆኖ  በወር 400 ሺህ ይከፈላቸዋል … አይደለም የሚከፈላቸው 250 ሺህ ብር ነው …. አይደለም 415 ሺህ የተጣራ ደመወዝ ነው የሚያገኙት  የሚሉ  የመረጃ ምንጮችን ዘገባ  አመራሮቹና አሰልጣኙ ማመንም ሆነ ማስተባበል ሳይችሉ ቀርተዋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የፈረሰኞቹ የመስመር ተከላካይ ወደ አዲስ አዳጊዉ ክለብ አምርቷል !!
Next Article ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋቾች የማበረታቻ ሽልማት ተካሄደ !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

በፊፋ ወርሃዊ ደረጃ ኢትዮጵያ 9 ደረጃዎችን አሻሻለች

hatricksport team By hatricksport team 9 years ago
ኢትዮጵያ ቡና የተከላካይ መስመር ተጫዋች አስፈርሟል!!
ሱራፌል ዳኛቸው በይፋ የሊጉ መሪን ተቀላቀለ
በ2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የዋንጫና የደረጃ ጨዋታዎች የዳኞችና የታዛቢዎች ሪፖርትን በመመልከት የተላለፉ ውሳኔዎች
ጅማ አባጅፋር ከ ሰበታ ከተማ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?