By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ተጠባቂዉ የደርቢ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል !
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ባህርዳር ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማ

የጨዋታ ዘገባ | ተጠባቂዉ የደርቢ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል !

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 1 year ago
Share
SHARE

 

በተስተካካይነት ተይዞ በነበረዉ እና በዛሬዉ ዕለት በተደረገዉ በሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ እና ፋሲል ከነማ 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት ጨዋታቸዉን አጠናቀዋል።

በ4-2-3-1 አሰላለፍ ወደ ጨዋታዉ የገቡት ባለሜዳዎቹ የጣና ሞገዶቹ በአምስተኛዉ ሳምንት ለገጣፎን ሁለት ለዜሮ ሲያሸንፉ ከተጠቀሙት አሰላለፍ የሁለት ተጫዋቾችን ለዉጥ አድርገው ወደ ሜዳ ሲገቡ በተቃራኒው አፄዎቹ በሳምንቱ አጋማሽ ቅዱስ ጊዮርጊስን ሲረቱ ከተጠቀሙት የሁለት ተጫዋቾችን ለዉጥ አድርገዉ በ433 አሰላለፍ ወደ ሜዳ ገብተዋል።

- ማሰታውቂያ -

በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ ፊሽካ የጀመረው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በጨዋታዉ የመጀመሪያ ደቂቃ ላይ ባለሜዳዎቹ ባህርዳር ከተማዎች በሜዳ ላይ እንቅስቃሴም ሆነ በሙከራ ረገድ የተሻሉ ነበሩ ማለት ይቻላል። በተቃራኒው አፄዎቹ በሙከራም ሆነ በሜዳ ላይ እንቅሰቃሴ ያን ያህል ነበሩ ማለት አይቻልም ነበር በዚህም በመጀመሪያው አጋማሽ ማለት በሚቻል መልኩ የበላይነት የነበራቸዉ ባህርዳሮች የጨዋታውን የመጀመሪያ ሙከራ በ10ኛዉ ደቂቃ ላይ ማድረግ ችለዋል። በዚህም ከፈቱዲን ጀማል የተሻገረለትን ኳስ የመስመር ተጫዋቹ ዱሬሳ ሹቤሳ እገፋ ሳጥን ዉስጥ ገብቶ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም በሳማኪ ሚካኤል ቅልጥፍና ኳሷን ተቆጣጥሯታል።

በተደጋጋሚ ወደ አፄዎቹ የግብ ክልል መድረስ የቻሉት ባህርዳር ከተማዎች በድጋሚ ከደቂቃዎች በኋላ ጥሩ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። በዚህም በ21ኛዉ ደቂቃ ላይ ይሁን እንዳሻዉ የአጥቂ አማካዩ ፉአድ ፈረጃ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተገኘዉን ቅጣት ምት ሰላምላክ ተገኝ በቀጥታ ወደ ግብ መቶ የነበረ ቢሆንም የአፄዎቹ የግብ ዘብ እንደምንም ኳሷን መልሷታል።

ከዕረፍት መልስ ከመጀመሪያዉ አጋማሽ በንፅፅር ተሻሽለዉ ወደ ሜዳ የተመለሱት አፄዎቹ በእንቅስቃሴም ሆነ በሙከራ ረገድ ተሻሽለዉ መመለሳቸውን ተገንዝበናል። በተለይ በ52ኛዉ ደቂቃ ላይ ጋይራ ዩፍ ከግራ መስመር ተከላካዩ ሔኖክ የቀማዉን ኳስ ለሽመክት አቀብሎት የመስመር ተጫዋቹ ኳሷን ቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም የጣና ሞገዶቹ ግብ ጠባቂዉ እንደምንም ኳሷን አዉጥቷታል።

ናትናኤል ዘለቀን እና ፍቃዱ አለሙን በጋይራ ዩፍ እና ሀብታሙ ገዛኸኝ ቀይረዉ ወደ ሜዳ ያስገቡት አፄዎቹ በተለይ የጨዋታው ሰዓት እየገፋ በመጣ ቁጥር በቀኝ መስመር እና በሜዳዉ የመሐል ክፍል ላይ ይጣሉ በነበሩ ኳሶች የግብ ዕድል ለማግኘት ሞክረዉ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸዉ ቀርተዋል።

በጨዋታዉ 70ኛ ደቂቃ ላይ አፄዎቹ ትልቅ የግብ ዕድል ቢያገኙም ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። በዚህም ያሬድ ባየ የፊት መስመር አጥቂዉ ፍቃዱ አለሙ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት የአፄዎቹ አምበል አስቻለዉ ታመነ ቢመታም ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

በሁለቱም ቡድኖች ረገድ ጨዋታዉን ለማሸነፍ ካላቸዉ ጉጉት የተነሳ በሚመስል መልኩ እስከ ጨዋታዉ መጠናቀቂያ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ ተቃራኒ የግብ ክልል መድረስ ቢችሉም ሁለቱም ቡድኖች ኳስ እና መረብን ማዋሀድ ሳይችሉ ቀርቶ ጨዋታዉ 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መንግስት ለእግርኳስ ትኩረት እንደሚሰጥ አረጋገጡ “ለእግርኳሳችን ለተሰጠው ትኩረትና ክብር እናመሰግናለን” አቶ ደረጄ አረጋ /የአ/አ እግርኳስ ፌዴ ፕሬዝዳንት/
Next Article በባህርዳር ከተማ ሲሰጠው የቆየው የካፍ ”C License የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቀቀ !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ጫላ ተሽታ አራተኛ ፈራሚ በመሆን ቡናማዎቹ ቤት ደርሷል

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 1 year ago
በጣም የሚወዷት እና ሁሌም የሚያነቧት ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ ለገበያ ትቀርባለች።
ፋሲል ከነማ የሁለቱን የዉጭ ሀገር ተጫዋቾች ዉል አድሷል።
ረቡዕ…ረቡዕ…ረቡዕ…ረቡዕ ሀትሪክ የመጀመሪያ ካደረጋት ባለቀለም ሀትሪክ ጋዜጣዋ በተጨማሪ ሀትሪክ በባለቀለም መፅሔትም መጣችልዎ!!
“የበፊቱን ሐዋሳ ከተማን ለመገንባት ጠንክረን እየሰራን ነው”ብሩክ በየነ /ሐዋሳ ከተማ/
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?