በመጪው ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቡና እና ወላይታ ድቻ መካከል የሚደረገው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታድየም እንደሚደረግ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ተናግረዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው ከጨዋታው ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ጋዜጣው መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም ጨዋታው በአዲስ አበባ ስታድየም እንደሚደረግ በማንሳት ቅሬታዎች ሲቀርቡበት የነበረው ስታድየሙ ከብሔራዊ ቡድኑ የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች በኋላ ማሻሻያዎች ተደርገውበታል ሲሉ ተናግረዋል።
ጨዋታው ከ9:00 ጀምሮ ሲደረግ የስታዲየሙ በሮች ከ6:30 ጀምሮ ክፍት ይሆናሉ። የመግቢያ ዋጋ በተመለከተ ክቡር ትሪቡን 500 ብር ፣ ጥላ ፎቅ 300 ብር ፣ ከማን አንሼ 200 ብር ፣ ካታንጋ 100 ብር እንዲሁም ዳፍ ትራክ እና ሚስማር ተራ 50 ብር መሆናቸው ተገልጿል።
- ማሰታውቂያ -
በመግለጫው 145 ሺህ ብር ወጪ የሆነበት እና በመከላከያ ፋውንዴሽን የተሰራ አዲስ ዋንጫ ይፋ የተደረገ ሲሆን ክብደቱ 9.8 ኪ.ግ ቁመቱ ደግሞ 40 ሴ.ሚ ነው።
በጨዋታው አሸናፊ የሚሆነው ቡድንም ዋንጫው የሚወስደው ይሆናል።