By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያዊቷ ቡዜ ድሪባ የቶሮንቶ ዋተርፍሮንት ማራቶን አሸናፊ ሆነች
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችአትሌቲክስToronto marathon

ኢትዮጵያዊቷ ቡዜ ድሪባ የቶሮንቶ ዋተርፍሮንት ማራቶን አሸናፊ ሆነች

Mussie Girmay
Mussie Girmay 2 years ago
Share
SHARE

በካናዳ ቶሮንቶ ለ22ኛ ግዜ በተካሄደው የቲ.ሲ.ኤስ ቶሮንቶ ዋተር ፍሮንት ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ቡዜ ድሪባ የሴቶቹ ውድድር አሸናፊ ስትሆን አዱኛ ታከለ በወንዶቹ ፉክክር ሁለተኛ ወጥቷል፡፡

በጣም የተቀራረበ ፉክክር የታየበት የሴቶቹ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ያሉትን ደረጃዎች ይዘው ያጠናቀቁበት ሆኗል፡፡ የሴቶቹ አሸናፊ የተለየችው በመጨረሻዎቹ ጥቂት ሜትሮች በተደረገ የፈጣን አጨራረስ ፉክክር ነበር፡፡ ከአስረኛው ኪሎ ሜትር ጀምሮ ተሳታፊ የነበሩት ስድስቱም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች (ቡዜ ድሪባ፣ ዋጋነሽ መካሻ፣ አፈራ ጎድፋይ፣ ፎዚያ ጀማል፣ መሰረት ገብሬ፣ እና ቦንቱ በቀለ) በመሪነት የውድድሩን አጋማሽ 01፡11፡01 በሆነ ሰዓት ያለፉት ሲሆን ይጓዙበት የነበረው ፍጥነትም የቦታውን ሪኮርድ ለማሻሻል የሚያስችል ነበረ፡፡ ከሰላሳ አምስተኛው ኪሎ ሜትር በኋላ ለአሸናፊነት የሚደረገው ፉክክር በአራቱ ኢትዮጵያውያን ቡዜ ድሪባ፣ ዋጋነሽ መካሻ፣ አፈራ ጎድፋይ፣ እና ፎዚያ ጀማል መካከል ነበር፡፡ አራቱ አትሌቶች በፊት መሪነቱ ስፍራ እየተፈራረቁ እስከመጨረሻው እግር በእግር ተከታትለው ከሄዱ በኋላ ፈጣን የአጨራረስ ብቃቷን የተጠቀመችው ቡዜ ድሪባ 2፡23፡11 በሆነ የራሷ ምርጥ ሰዓት አንደኛ ወጥታለች፡፡ ከቡዜ ጋር የመጨረሻውን ፉክክር ያደረገችው የዘንድሮ የኦታዋ ማራቶን አሸናፊዋ ዋጋነሽ መካሻ በ2፡23፡12 የሁለተኛነቱን ደረጃ ይዛ ስታጠናቅቅ አፈራ ጎድፋይ በ2፡23፡15 ሶስተኛ ወጥታለች፡፡ ፎዚያ ጀማል (2፡23፡18)፣ መሰረት ገብሬ (2፡29፡54)፣ እና ቦንቱ በቀለ (2፡31፡33) በቅደም ተከተል አራተኛ፣ ሰባተኛ እና ዘጠነኛ ሆነው ጨርሰዋል፡፡ ቡዜ ሶስተኛ የማራቶን ውድድሯን ባደረገችበት የቶሮንቶ ውድድር ላይ በማራቶን የመጀመሪያ የአሸናፊነት ውጤት ከማስመዝገቧ በተጨማሪም የራሷን ምርጥ ሰዓት በ4 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ አሻሽላለች፡፡

ከስድስት ዓመት በላይ መቀመጫዋን በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ኒው ሜክሲኮ አድርጋ የቆየችው ቡዜ ከአንድ ዓመት በፊት ወደኢትዮጵያ በመመለስ በአሰልጣኝ ገመዱ ደደፎ ስር ስትሰለጥን ቆይታለች፡፡ ለዘንድሮው የቶሮንቶ ማራቶን ዝግጅት ከመጀመሯ በፊት ባለፈው ግንቦት ወር በፔንሲልቬንያ የተካሄደው ፒትስበርግ ግማሽ ማራቶን አሸናፊ ስትሆን በነሐሴ ወር በማሳቹሴትስ ፋልመዝ በተካሄደ የሰባት ማይል የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳትፎዋ ስድስተኛ ወጥታለች፡፡ የማራቶን የዓለም ሻምፒዮኗ አማኔ በሪሶ እና የርቀቱ የዓለም ሪኮርድ ባለቤት ትግስት አሰፋ በሚሰለጥኑበት ስብስብ ውስጥ የተዘጋጀችው ቡዜ ከቶሮንቶ ድሏ በኋላ በሰጠችን አስተያየት ‹‹ትንሽ ነፋስ እና ቅዝቃዜ የነበረ ቢሆንም ከዚህ ቀደምም በመሰል ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ውስጥ የመወዳደር ተሞክሮ ስለነበረኝ ብዙም አልተቸገርኩም፡፡ ወደ ውድድሩ የመጣሁት የራሴን ምርጥ ሰዓት አሻሽላለሁ ብዬ ነበረ፡፡ አራት ሆነን ወደውድድሩ መጨረሻ ስንቃረብ ከተፎካካሪዎቼ ትንሽ የተሻለ የአጨራረስ ብቃት እንዳለኝ ስላሰብኩ እንደማሸንፍ ተሰምቶኛል›› ብላለች፡፡

በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ሆና ያጠናቀቀችው አፈራ ጎድፋይም ውድድሩን ለማሸነፍ አቅዳ መምጣቷን ጠቅሳ ‹‹አራት ሆነን ተያይዘን ወደመጨረሻው በተቃረብን ግዜ የተሻለ የአጨራረስ ብቃት ያላት ቡዜ ልታሸንፍ እንደምትችል አምኛለሁ እናም የሁለተኛነቱን ደረጃ ለማግኘት የምትችለውን ያህል ሞክሬያለሁ፡፡ ሆኖም ያም ሳይሳካ ሶስተኛ ሆኜ ልጨርስ በቅቻለሁ›› ብላለች፡፡

- ማሰታውቂያ -

በወንዶቹ ፉክክር ባለፈው ሚያዝያ ወር ቪዬና ላይ ባደረገው የመጀመሪያ የማራቶን ተሳትፎው ሰባተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኬንያዊው ኤልቪስ ኪፕቾጌ ቼቦይ በርቀቱ የመጀመሪያ ድሉን ቶሮንቶ ላይ ለማስመዝገብ በቅቷል፡፡ ኬንያዊው ያሸነፈበት 2፡09፡20 የሆነ ሰዓትም የራሱን ምርጥ ሰዓት በአንድ ደቂቃ ከአንድ ሰከንድ ያሻሻለበት ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያዊው አዱኛ ታከለ በ2፡10፡26 ሁለተኛ ሆኖ ሲጨርስ በርቀቱ የመጀመሪያ ውድድሩን ያደረገው ኬንያዊው አልፍሬድ ሙክቼ ኪፕቺርቺር በ2፡10፡56 ሶስተኛ ወጥቷል፡፡ ኢትዮጵያዊው ዮሀንስ መካሻ በ2:13:47 አራተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ኢትዮጵያውያኑ መንግስቱ ዘላለም ከ21 ኪሎ ሜትር በኋላ እና አብደላ ጎዳና ከ30ኛው ኪሎ ሜትር በኋላ ውድድሩን አቋርጠዋል።


በወንዶቹ ውድድር ላይ በሁለተኛነት የጨረሰው ኢትዮጵያዊው አዱኛ ታከለ ከውድድሩ በኋላ በሰጠው አስተያየት ‹‹አሯሯጮቹ መጀመሪያ ላይ ትንሽ ከማፍጠናቸው ውጪ ውድድሩ ጥሩ ነበር፡፡ ንፋስ በነበረበት የመወዳደሪያ ስፍራ በኪሎ ሜትር ሁለት ደቂቃ ከሀምሳ ሰባት ሰከንድ እየሄዱ የነበረ መሆኑ ጥሩ አይደለም፡፡ እንደዛም ሆኖ ሁለተኛ መውጣት በመቻሌ ደስተኛ ነኝ፡፡ የማሸነፍ ግብን ይዤ ብመጣም ንፋሱ እና የአሯሯጮቹ ፍጥነት ያሰብኩትን እንዳላሳካ ትንሽ ተፅዕኖ ፈጥሮብኛል፡፡ ለዚህ ውድድር ጥሩ ስዘጋጅ የነበረ ቢሆንም በመሐል የአኪለስ ሕመም ያስቸግረኝ ነበረ፡፡ በዚህም ምክንያት የፍጥነት ልምምድ እንደፈለግኩ አልሰራም ነበረ፡፡ የፍጥነት ልምምዱን እንደፈለግኩ ብሰራ ኖሮ ልጆቹ በፍጥነት ሲሄዱ አብሬያቸው መሄድ እችል ነበረ፡፡ ግን በደንብ ስላልሰራሁ ያንን መቋቋም አልቻልኩም›› ብሏል፡፡

በውድድሩ ላይ በወንዶች ከ2:07:00 በታች በሆነ ሰዓት ለሚጨርስ አሸናፊ እና በሴቶች ከ2:22:30 በታች በሆነ ሰዓት ለምትጨርስ አሸናፊ ይሰጣል ተብሎ የነበረውን 5,000 የካናዳ ዶላር የሰዓት ጉርሻ በሁለቱም ፆታዎች ያሳካ አልተገኘም፡፡


በሁለቱም ፆታዎች ውድድሩን ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ባሉት ደረጃዎች ውስጥ ሆነው ያጠናቅቁ አትሌቶች በደረጃ ቅደም ተከተላቸው መሰረት ተከታዩን የገንዘብ ሽልማት በካናዳ ዶላር የሚያገኙ ይሆናል፡፡

1 ኛ – 20,000 ዶላር

2 ኛ – 10,000 ዶላር

3 ኛ – 7,000 ዶላር

4ኛ – 4,000 ዶላር

5ኛ – 3,000 ዶላር

6 ኛ – 2,000 ዶላር

7ኛ – 1,500 ዶላር

8 ኛ – 1,000 ዶላር

©️ BIZUAYEHU TESFU WAGAW

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Mussie Girmay
Follow:
Managing Editor at Hatricksport Website
Previous Article የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ም/ል ሃላፊ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ቢኒያም ምሩጽን እንዲታገድ ሜድረጉ ቅሬታ ቀሰቀሰ
Next Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የዝውውር ዜናዎችዜናዎችሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

ሙሉአለም መስፍን /ዲኮ/ ሲዳማ ቡናን ተቀላቀለ

hatricksport team By hatricksport team 5 years ago
የጨዋታ ዘገባ | በከፍተኛ ግለት የተደረገው የባህርዳር ከተማ እና የድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል
የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ የዕጣ ማውጣት እና ዓመታዊ ግምገማ ተካሄደ
“ተጨዋቾቼ ለውጥ ቢኖራቸውም ከ7 ወራት በፊት ወደነበሩበት አቋም አሁንም አልተመለሱም” አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
“በዚህ ልክ ተፅዕኖ እፈጥራለሁ ብዬ አልጠበኩም” “የውል ማፍረሻ እንክፈል ብለውኝ ነበር” “አምስት ወራትን ከጨዋታ መራቅ ከባድ ነው” “እንደመጣሁ ጨዋታ አለማድረጌ ጠቅሞኛል” “በጣም እያለቀስኩ ነበር” አረጋሽ ካልሳ – ያንግ አፍሪካ (ያንጋ ፕሪንሰስ)
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?