By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ ቡናና ቤቲካ ኢትዮጵያ ውላቸውን አራዘሙ
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችቤቲካ

ኢትዮጵያ ቡናና ቤቲካ ኢትዮጵያ ውላቸውን አራዘሙ

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
Share
SHARE

 

****በየአመቱ 6 ሚሊዮን በወር 500ሺህ ብር…..
****የዛሬ አራት አመት በተጠና ጥናት ሊጉ 2.2 ቢሊዮን ወጪ ነበረው አሁን ደግሞ በጣም ጨምሯል..

“አክሲዮን ማህበሩ ከክለቦች በላይ አይደለም አዲሱ ውል ከቡና ባንክ ጋር ያለንን ውል የሚነካ ከሆነ በፍጹም አንቀበልም”

“በቤትኪንግ ምክንያት ማግኘት ያለብንን ጥቅም አጥተናል … አሁን ግን በፍጹም አንፈቅድም”

- ማሰታውቂያ -

አቶ ገዛኧኝ ወልዴ
የኢትዮጵያ ቡና ዋና ስራአስኪያጅ

“በእኛ በኩል ማግኘት ያለብንን አግኝተናል ብለን ባናምንም አላኮረፍንም አሁን ግን የምንካካስበት ጊዜ ነው”

“ያልተተገበረ ውል ስላለ ጥለን አንሄድም ከነገ ጀምሮ ግን ጥቅማችንን ማግኘት እንጀምራለን ”

አቶ አብርሃም ተ/ማሪያም
የቤቲካ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ

 

ኢትዮጵያ ቡና ከ8 ሀገራት ጋር የስፖርት የውርርድ ስራዎችን እየሰራ ካለው ቤቲካ ኢትዮጵያ ጋር የነበራቸውን ውል ለተጨማሪ ሶስት አመታት አራዝሟል።

ዛሬ ጠዋት በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል በተካሄደው የፊርማ ስነስርዓት ላይ የኢትዮጵያ ቡናው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኧኝ ወልዴ እንደተናገሩት ” ከቤቲካ ጋር የባለፉት ሁለት አመት ሂደቶችን ገምግመናል። ከሊጉ ጋር ውል የገባው ቤትኪንግ ስለነበር የቤቲካ መብት በተወሰነ መልኩ ተገድቦ ቆይቷል። የቀጥታ ስርጭት ላይ የቤቲካ አርማን ማስተላለፍ አንችልም ነበር አሁን ግን ህግና ስርአቱን ተከትለን ለማስተዋወቅ ተዘጋጅተናል ከቤቲካ ጋር ቁጭ ብለን ከተነጋገርን በኋላ ውሉን እንደገና ለቀጣዮቹቹ 3 አመታት አድሰነዋል አሁን የተገደበ ነገር ሳይኖር ቤቲካ ማግኘት ያሉበት መብቱ ሁሉ ይከበራል ባለፉት አመታት በቤትኪንግ ምክንያት ማግኘት ያለብንን ጥቅም አጥተናል … አሁን ግን ይህ እንዲሆን አንፈቅድም” ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ገዛኧኝ እንደገለጹት ” ከቤቲካ ጋር ከጥቅምት 2016 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 2018 ድረስ ውላችንን አድሰናል ነገር ግን ከክፍያው ጋር ተያይዞ በየአመቱ እንነጋገራለን
ባለፉት ሁለት አመታት እንደነበረው በአመት 6ሚሊየን ብር ይከፍሉናል ከሁለቱ አመት የሚለየው ግን በአሁኑ ውል በየወሩ 500ሺ የሚከፈለን መሆኑ ነው ክለቡ የሚያስመዘግበው ውጤትና በየጊዜው ያለውን የዋጋ ግሽበት ላይ ለመነጋገር በየአመቱ መጨረሻ ባለው ጉዳይ ላይ እንወያያለን”ሲሉ አስረድተዋል። ፕሪሚየር ሊጉ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተስማማ እናንተ ቡና ባንክ ጋር ካላችሁ ውል አንጻር እንዴት ለማስኬድ አስባችኋል..? የተባሉት አቶ ገዛኧኝ አጽንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት
“ሼር ካምፓኒው 16 ክለቦች ቆርሰው የሰጡትን መብት ነው እየተገበረ ያለው … ሁሉም ክለቦች መብት አላቸው ክለባችን ማግኘት ያለበት ጥቅም በሊግ ኩባንያው እንዲቀር አንፈቅድም… በቤትኪንግ ምክንያት ማግኘት ያለብንን አጥተናል አሁን ግን አንፈቅድም። የኛን ጥቅም ባልነካ መልኩ ኩባንያው መወያየት መፈራረም ይቻላል ..የስፖንሰሮቻችንን ፍላጎትና ጥቅማቸውን ማክበር አለብን የትኛው ስፖንሰር የክለባችንን ጥቅም ካላስከበረ አንቀበልም “ሲሉ መልሰዋል።

የሊጉ የፊይናንስ ስርዓትና የክለቦች ደመወዝ መክፈል አለመቻል የሚፈጥረው አደጋ ዙሪያ የተጠየቁት አቶ ገዛኧኝ ” የሀገሪቱ ሊግ ከፋይናንስ ስርዓቱ ጋር ተያይዞ ስርዓተ አልበኝነት የነገሰበት ነው የዛሬ አራት አመት በተጠና ጥናት ሊጉ 2.2 ቢሊዮን ወጪ ነበረው። አሁን ደግሞ ከዚህም ይጨምራል በመንግስት የሚደጎሙት ክለቦች የገንዘብ ችግር ያን ያህል ላይጎዳቸው ይችላል ከስፖንሰር ሰብስበው ለሚንቀሳቀሱ ክለቦች ግን አደጋ ነው በርግጥ በኛ በኩል የፋይናንስ ችግር ውስጥ ሆነን የደመወዝ ክፍያ ጥያቄ አልተነሳንም ነገር ቀጣይ አመታቶች ያሰጉናል እንደ ክለባችን ቦርድ ውሳኔ ከቀጣዩ አመት ጀምሮ በወጣት ተጨዋቾች ላይ እንሰራለን
ዘንድሮ ከ11 ቋሚ ተጨዋቾች አምስቱ ከቢ ያደጉ ናቸው እነሱም የ4 አመት ውል ያላቸው ናቸው። ሊጉ ብዙ የገንዘብ ኔቴወርክ ሰንሰለትም አለው እንዲቀጥል ከተፈለገ መንግስት ዞር ብሎ ሊያየው ይገባል” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። ከራይድ ጋር ስላለው ግንኙነት የተጠየቁት አቶ ገዛኧኝ “ከራይድ ጋር በገባነው ውል መሠረት ማግኘት ያለብን 100 ፐርሰንት ክፍያን ወስደናል ያም ሆኖ ያለው ውሉ በመጠናቀቁ ተለያይተናል” ሲሉ ተናግረዋል።

የቤቲካ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አቶ አብርሃም
ተ/ማሪያም በበኩላቸው ህዝባዊ መሠረት ያለው ክለብ ጋር ውላችንን በማደሳችን ክብር ይሰማናል ቤቲካ ከተለያዩ ማህበራዊ ስራና መዝናኛው ላይ እየሰራ ነው በአሁኑ ስምምነትም ደስ ብሎናል….አምና ወደ 15 የውርርድ ተቋማት ሂሳባቸው ታግዶ ነበር እዚያ ችግር ውስጥ ሆነንም እንኳን ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ያለንን ውል ስናክብር ቆይተናል በእኛ በኩል ባለፉት ሁለት አመታት ማግኘት ያለብንን አግኝተናል ብለን ባናምንም አላኮረፍንም አሁን ግን የምንካካስበት ጊዜ ነው በእስካሁኑ ውል ያልተተገበረ ነበር ብለንም ጥለን አንሄድም ከነገ ጀምሮ ግን ጥቅማችንን ማግኘት እንደምንጀምር ተስፋ አደርጋለሁ ኢትዮጵያ ቡና ያለው ግንኙነት ቤተሰባዊ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ቡናና የቤቲካ ኢትዮጵያ የውል ዕደሳውን በቤቲካ በኩል ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ አብርሃም
ተ/ማሪያምና የኢትዮጵያ ቡና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኧኝ ወልዴ በፊርማቸው አጽድቀውታል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ”ለእኔ ከግል ስኬት ይልቅ የቡድን ስኬት ይበልጥብኛል” ”እዉነት ነዉ የቅዱስ ጊዮርጊስን ማለያ ለብሶ ሁለተኛ መዉጣት አይቻልም” ”ለብሄራዊ ቡድን ብዙ ላደርግ እፈልጋለሁ” ቢኒያም በላይ /የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋች/
Next Article የአመቱ ኮከብ ተመራጮች የሽልማት ገንዘብ አለመከፈሉ አነጋጋሪ ሆኗል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቁጥሮች

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ዙር ቁጥራዊ መረጃዎች – ክለቦች

Habtamu Mitku By Habtamu Mitku 3 years ago
ጅማ አባጅፋር ከ ሰበታ ከተማ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
የመጀመሪያዋ ባለቀለምና ተወዳጇ ሀትሪክ ሳምንታዊ የስፖርት ጋዜጣ እንደተለመደው አዳዲስና ትኩስ ዘገባዎችን አካታ ነገ ማለዳ እጅዎ ትገባለች ይጠብቃት
የ2011 ኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ በቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/ ይከታተሉ
ሪፖርት | አዳማ ከተማ ወልዋሎን በማሸነፍ ደረጃውን ማሻሻል ችሏል።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?