By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የፋሲል ከነማ ቦርድና ተሰናባቹ አሰልጣኝ ሃይሉ ነጋሽ ሳይስማሙ ተለያዩ
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከነማ

የፋሲል ከነማ ቦርድና ተሰናባቹ አሰልጣኝ ሃይሉ ነጋሽ ሳይስማሙ ተለያዩ

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 11 months ago
Share
SHARE

► የቦርድ አባሉ አቶ ሀብታሙ አዱኛ የልቀቁኝ ደብዳቤ
አስገብተዋል..

► በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ መንገድ ላይ
አሰልጣኝ ሃይሉ ነጋሽ /ቲጋና/ ቆሟል

► ቅጥሩ ይፋ ባይሆንም አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ
የክለቡን ተጨዋቾች አግኝቷል

የፋሲል ከነማ ቦርድ ከተሰናባቹ አሰልጣኝ ሃይሉ ነጋሽ
/ቲጋና/ ጋር ያደረገው ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል።

- ማሰታውቂያ -

ትላንት ከቀትር በፊት ሁለት የክለቡ የቦርድ አባላት ከአሰልጣኝ ሃይሉ ጋር የተወያዩ ሲሆን ክለቡ እስከ ሰኔ ያለውን ደመወዝ ሊከፍለው እሱም ከተሰናበተበት ቀን ጀምሮ ያልሰራበትን ቆጥሮ የፊርማ ክፍያውን እንዲመልስ ቦርዱ መወሰኑን ገልጸውለታል። አሰልጣኙም በበኩሉ በራሱ ምክንያት አለመሰናበቱን አሰናባቹ ቦርዱ መሆኑን፣ ውጤት በማጣት ተሰናብቻለሁ ብሎ እንደማያምን ሌሎች የቀረቡለትን የሶስት ክለቦች ጥያቄ ወደጎን ማለቱን በመግለጽ የተሰጠውን የፊርማ ክፍያ ለመመለስ እንደማይችል አቋሙን ግልጽ አድርጎላቸው ሳይስማሙ ቀርተዋል። አመራሮቹ ኦዲት እንደሚደረጉና ክፍተቱ እንደሚያስጠይቃቸው በመግለጽ የፊርማ ክፍያውን ቀሪ ገንዘብ መክፈሉ እንደማይቀር በዚህ ካልተስማማ ወደ ክርክር መግባታቸው እንደማይቀር ጠንከር ባለ መልክ መግለጻቸውን ከታማኝ ምንጭ የተገኘ መረጃ ያስረዳል። አሰልጣኝ ሃይሉም የፊርማ ክፍያውን እንደማይመልስ የስድስት ወር ደመወዙን ግን ከክለቡ እንደሚጠብቅ የማይቀየር አቋሙ መሆኑን በመግለጹ የሁለቱ ወገኖች ስብሰባ ያለ ስምምነት መጠናቀቁ ታውቋል።

አመራርቹ ከአሰልጣኝ ሃይሉ ጋር ያለውን ልዩነት ቋጭተው የአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ቅጥርን ይፋ ለማድረግ ቢጥሩም በአሰልጣኝ ሃይሉ ጠንካራ አቋም ሳይሳካ ቀርቷል። የአሰልጣኝ አሸናፊ ቅጥር ይፋ ባይደረግም ግን አሰልጣኝ አሸናፊ ከፋሲል ከነማ ተጨዋቾች ጋር ልምምድ መጀመሩ ታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የክለቡ የመሃል አስቻለሁ ታመነ ክለቡን ለመልቀቅ በደብዳቤ ጠይቋል የሚለው መረጃ ውሸት መሆኑ ታውቋል። ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ ተጨዋቹን ጨምሮ የክለቡ አምበሎች ቡድኑን በሚገባ አልረዳችሁም ተብለው አምበልነታቸው ሲነጠቅ አስቻለሁ ካልፈለጋችሁን አልረዳችሁም ካላችሁ መልቀቂያ ስጡንና አሰናብቱን ማለቱ ታውቋል ።ከዚያ ውጪ የወጣው ደብዳቤ አስገብቷል መረጃ ውሸት መሆኑና ተጨዋቹ ውሉን የሚያከብር መሆኑን ማሳወቁን ታማኝ ምንጩ ገልጿል።

የቡድን መሪው ሀብታሙ ዘዋለን የሃላፊነት መልቀቅ ጥያቄ ያልተቀበለው የፋሲል ከነማ ቦርድ ከሌላው የቦርድ አባል የልቀቁኝ ጥያቄ ቀርቦለታል። የቦርድ አባሉ አቶ ሀብታሙ አዱኛ ባለብኝ የስራ መደራረብ ክለቡን ማገልገል ባለመቻሌ ከቦርድ አሰናብቱኝ ሲሉ ደብዳቤ አስገብተዋል።
አቶ ሀብታሙ “ባለብኝ የግል ስራ የፕሮጀክት መብዛትና ተደራራቢ ስራ የተነሳ በበርካታ የቦርድ ስብሰባ ላይ መገኘትና ክለቡን በሚጠበቅብኝ ልክ ማገልገል አለመቻሌ ይታወቃል አሁንም የሚጠበቅብኝን ሃላፊነት በበቂ ሁኔታ እወጣለሁ ብዬ ስለማላምን በቂ ጊዜ አግኝቶ ክለቡን በሚያገለግል ሰው እንድትተኩኝ እጠይቃለሁ። ነገር ግን ከቦርድ ውጪ ሆኜ የከተማዬን ክለብ በሚፈለግብኝ መጠን ለማገዝ ዝግጁ ነኝ ” ሲሉም ጥር 1/2015 ባስገቡት የልቀቁኝ ደብዳቤ ጠይቀዋል።

አጼዎቹ ፋሲል ከነማዎች በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ17ጥብና 2 ግብ በሊጉ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article 12ኛው የአዝናኙ ሲዝናና የሚዲያ ካፕ ቅዳሜ ሊጀመር ነው
Next Article መንግስት ለፌዴሬሽኑ 15 ሚሊዮን ተጨማሪ በጀት ፈቀደ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግድሬዳዋ ከተማ

ድሬዳዋ ከተማ ለአንድ ተጫዋች ማስጠንቀቅያ ሰጥቷል።

ሚሊዮን ኃይሌ By ሚሊዮን ኃይሌ 4 years ago
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የደቡብ ሱዳን ጨዋታ አሰመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል
ፈረሰኞች አዲስ አሰልጣኝ ሾመዋል !
ሲዳማ ቡና የአማካይ ስፍራ ተጫዋች አስፈርሟል !!
ኢትዮጵያ ቡናና ሀበሻ ቢራ የፈጠሩትን ግንኙነት ዳግም አድሰዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?