By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ ቡና ጎልደን ድራገንን የተሰኘውን ዘመናዊ አውቶቢስ ተረከበ
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና ጎልደን ድራገንን የተሰኘውን ዘመናዊ አውቶቢስ ተረከበ

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
Share
SHARE

“ባለፉት አመታት አምጠን አምጠን ዛሬ ተወልዷል በዚህም በጣም ተደስተናል”
መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ
/ የኢትዮጵያ ቡና የቦርድ ፕሬዝዳንት/

ኢትዮጵያ ቡና ከክለቡ ዋነኛ አጋር ከሆነው ሀበሻ ቢራ አክሲዮን ማህበር ዘመናዊ የተጨዋቾች ማመላለሻ መኪና ዛሬ ተበረከተለት ።

ዛሬ ከቀትር በኋላ በካሌብ ሆቴል በነበረው የርክክብ ስነስርዓት ላይ ” የሰርቪሱ ስጦታ ቃል ከተገባ 5 አመት ያለፈው ሲሆን ባለፉት አመታት አምጠን አምጠን ዛሬ ተወልዷል በዚህም በጣም ተደስተናል። ደጋፊው ቃል ተገብቶ ሳይሰጠን እያለ ለሚያነሳው ጥያቄም ምላሽ በመሆኑ ትልቅ ደስታ የሚፈጥር ነው ዘመናዊ አውቶቢሱ ብዙ ካገለገለ ለአምስት አመታት ነው ከዚያ በኋላስ የሚለው ከአሁኑ መታሰብ አለበት ማናጅመንቱ ቢኖርም ባይኖርም ኢትዮጵያ ቡና ዘላለማዊ በመሆኑ ከፍ ወዳለ ስራ መግባት አለብን… ሰርቪሱ ላይ የኢትዮጵያ ቡናና የሀበሻ ቢራ ሎጎዎች መደረጉ ከደጋፊው ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ነው” ሲሉ የክለቡ የቦርድ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ተናግረዋል።

- ማሰታውቂያ -

“ሀበሻ ቢራ አክሲዮን ማህበር በራሱ አነሳሽነት ከውል ውጪ መኪናውን መግዛቱ ከእኛ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ የመሄድ ፍላጎቱን ያሳያል ወደ 6 ሚሊዮን የሚጠጋ ደጋፊያችን ከተቋሙ ጎን እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ…. ለዘመናዊው አውቶቢስ ግዢ የተመበው 23 ሚሊዮን ብር ቢሆንም መኪናው የተገዛው በ17 ሚሊዮን 500 ሺህ ብር ነው ለዚህም በክለባችን ቦርድ ማኔጅመንትና ደጋፊው ስም አመሰግናለሁ” ሲሉ መቶ አለቃ ፈቃደ ተናግረዋል።

የክለቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኧኝ ወልዴ በበኩላቸው “ላለፉት አምስት አመታት እየተንከባለለ የዋጋ ንረት ሲከሰት በጀቱን እየጨመርን እዚህ ደርሰናል። የዘመናዊው መኪና ግዢው በመፈጽሙ ደስ ብሎናል ክለባችን በፋይናንስ ግልጽ ሆኖ ሙሉ መረጃውን ገቢና ወጪውን የተጨዋቾች ደመወዝ ሳይቀር የሚገልጽ መሆኑ ይታውቃል በዚህ ግዢ የመጀመሪያ ተመስጋኝ ሹፌራችን ነው መኪናው ያለበትን ቦታ ሄዶ አይቶ ፕሮፎርማ አምጥቶ ነው ግዢው የተፈጸመው …መኪናውን የገዛነው ከበላይነህ ክንዴ አስመጪ ድርጅት ሲሆን እኛ መሆናችንን ካወቀ በኋላ ሂሳቡን ቀንሶ ሽያጩን ስላደረገልን እናመሰግናለን” ሲሉ አስረድተዋል። አቶ ገዛኧኝ ጨምረው ሲናገሩ ” የመኪናው ግዢ ከታክስ ጋር 17 ሚሊዮን 500 ሺህ ብር ሲሆን ለተለያዩ የግዢ ሂደቶች ወደ 850 ሺህ ብር ተጨማሪ ወጪ ሆኖ አጠቃላይ ግዢው 18 ሚሊዮን 83 ሺህ 647 ብር አካባቢ ሆኗል ” ሲሉ አብራርተዋል።

ከጫሹ ከበላይነህ ክንዴ አስመጪ ድርጅት ተወክለው የመጡት አቶ ሃይሉ ዘርጋው በበኩላቸው “ኢትዮጵያ ቡና በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ በመጀመሪያ ረድፍ ከሚጠሩት አንዱና አንጋፋ ክለብ ነው … ከዚህ ታሪካዊ ክለብ ጋር ግንኙነት በመፍጠራችን ደስ ብሎናል መኪናው ጎልደን ድራገን ባስ ሲሆን በዘመናዊነቱና ዋጋው ከአውሮፕላን ዝቅ ከመደበኛ አውቶቢሶች ከፍ ያለ ነው ይህን መኪና አዲሱ ደንበኛችን የሆነው ኢትዮ ቡና መረከቡ ትልቅ እመርታ ነው የድርጅቱም ባለቤት አቶ በላይነህ የሚገዛው ኢትዮጵያ ቡና ከሆነ 500 ሺህ ብር ቀንሱ ብለው አዘውን ነው ሽያጩ የተከናወነው” ሲሉ ተናግረዋል

የኢትዮጵያ ቡና የስራ አመራር ቦርድ አባል የሆኑት አቶ ይስማሸዋ ስዩምም በዕለቱ እንደተናገሩት ” ከሀበሻ ቢራ አክሲዮን ማህበር ጋር የነበረን የግንኙነት ጅማሮ 10 አመታት ያልፈዋል ያኔ የተተከለውን ግንኙነት ያሳደጉት አሁን ያሉት ናቸው … ሀበሻ ቢራ አክሲዮን ማህበር ገና ጠርሙስ ማምረት ሳይጀምር ነው ከኛ ጋር ግንኙነት የጀመረው…. የክለባችንን ሩጫ ጨምሮ በርካታ ኢቨንቶች ላይ ድጋፍም ሲያደርግ ኖሯል.. ኢትዮጵያ ቡናም ለሀበሻ ታማኝ ደንበኛ በመሆኑ ሀበሻ ከጭንቅላታችን አይወጣም” ሲሉ አስረድተዋል።

አቶ ይስማሸዋና መቶ አለቃ ፈቃደ የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት ሲጀመር የሀበሻ ቢራ አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩትና አሁን በህይወት የሌሉትን አቶ ዘውዱ ንጋቱን ከግንኙነቱ ጅማሮ አንስቶ ለነበራቸው ተነሳሽነትና ድጋፍ በክለባቸው ስም አመስግነዋል።

ደጋፊውን በመወከል ንግግር ያደረጉት የደጋፊ ማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ መንግስቱ ታደሰ በበኩላቸው ” የኢትዮጵያ ቡናና የሀበሻ ቢራ አክሲዮን ማህበር ግንኙነት ቤተሰባዊ ነው በርካታ ጊዜ የፈጀብን ጉዞ በመጠናቀቁ እንዲሁም የደጋፊው ህልም በመሳካቱ ደስ ብሎኛል ደጋፊያችን የሀበሻ ማርኬቲንግ በመሆን ከተቋሙ ጎን እንደሚሆን እተማመናለሁ” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

17 ሚሊዮን 500 ሺህ ብር ወጪ የተደረገበት ጎልደን ድራገን ባስ ከሹፌሩና ረዳቱ ጋር 53 ሰዎችን የሚይዝ መሆኑ ታውቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካውንት ታገደ
Next Article ወልቂጤ ከተማ ከዝውውር መስኮት ታገደ….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግLIVESCORE

የ2011 ኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ በቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/ ይከታተሉ

Fitsum Nigusse By Fitsum Nigusse 7 years ago
ቡናማዎቹ የወሳኝ ተጫዋቻቸውን ውል አራዘሙ
ቅድመ ዳሰሳ | ወልዋሎ አዲግራት.ዮ ከ ሀድያ ሆሳእና
የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ በሄኖክ አዱኛ ብቸኛ ግብ ከጦና ንቦቹ ሶስት ነጥብ ወስደዋል
የአዲስ አበባ ስታዲየምን እድሳት ለማድረግ የውል ስምምነት ተካሄደ ።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?