By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የሸገር ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቅዱስ ጊዮርጊስየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

የጨዋታ ዘገባ | የሸገር ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በይደር ቆይቶ የተደረገው 46ኛው የሸገር ደርቢ በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቋል ።

በጨዋታው ኢትዮጵያበ ቡና በኩል በረከት አማረ ፣ ራምኬል ጀምስ ፣ ወልደአማኑኤል ጌቱ ፣ ሃይለሚካኤል አደፍርስ ፣ ቃልአብ ፍቅሩ ፣ ሬድዋን ናስር ፣ አማኑኤል ዮሐንስ ፣ አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ ፣ መስፍን ታፈሰ ፣ ሮቤል ተክለሚካኤል እና ብሩክ በየነ በመጀመሪያ አሰላለፍ ሲካተቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል ባህሩ ነጋሽ ፣ ፍሪምፖንግ ሜንሱህ ፣ ምኞት ደበበ ፣ ሄኖክ አዱኛ ፣ ረመዳን የሱፍ ፣ ጋቶች ፓኖም ፣ ናትናኤል ዘለቀ ፣ ቢንያም በላይ ፣ አቤል ያለው ፣ ቸርነት ጉግሳ እንዲሁም እስማኤል ኦሮ አጎሮ በምርጥ አስራ አንድ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው ።

ከጨዋታው መጀመር አስቀድሞ ለበርካታ ዓመታት በፕሪሚየር ሊጉ እና በአለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በዳኝነት ላገለገለችው ኢንተርናሽናል አርቢትር ሊድያ ታፈሰ የሽኝት ፕሮግራም ተደርጓል ። አርቢትሯን ከሙያ ባልደረቦቿ በተጨማሪም የሁለቱም ክለብ ደጋፊዎች በክብር ሸኝተዋታል ።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ ያደረገበት ሆኖ አልፏል ።

በአጋማሹ በፈረሰኞቹ በኩል በተለይም ከቀኝ መስመር በሚነሱ ኳሶች የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል ።

በኢትዮጵያ ቡና በኩል ለረጅም ደቂቃዎች ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ የግብ ክልል ለመድረስ ተቸግረው ቆይተዋል ። በተለይም የፊት መስመሩን ሲመራ ለነበረው ብሩክ በየነ በረጅም ሲላኩ የነበሩ ኳሶች በቀላሉ በቅዱስ ጊዮርጊስ ተከላካዮች እግር ስር ይገቡ ነበር ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ሙከራ በስምንተኛው ደቂቃ ላይ የተደረገ ሲሆን አቤል ያለው ከቢንያም በላይ የደረሰውን በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ሆኖ ወደ ግብ ሞክሮ ለጥቂት ወደ ውጪ ወቶበታል ።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላም ፈረሰኞቹ ጫና ባበዙበት የቀኝ መስመር ቢንያም በላይ ይዞ የገባውን ኳሶ ለመቀነስ ያደረገው ጥረት ተቀባይ ባለማግኘቱ ሳይሳካ ቀርቷል ።

በ4 – 1 – 4 – 1 ቅርፅ ወደ ሜዳ የገባው የአሰልጣኝ ዮሴፍ ኢትዮጵያ ቡና በነዚህ ደቂቃዎች ላይ በተለይም ናትናኤል ዘለቀ ከኋላ እየተቀበለ ወደ ፊት የሚጥላቸውን ኳሶች ለመቆጣጠር ተቸግረው ቆይተዋል ።

ቡናማዎቹ ከኋላ መስርተው ይዘው የሚያወጧቸው ኳሶችም ወደ ፊት በሚደርሱበት ጊዜ ለፈረሰኞቹ ተከላካዮች ጫና የማይፈጥሩ ነበሩ ።

ለፈረሰኞቹ አጥቂ እስማኤል ኦሮ አጎሮ የሚደርሱ ኳሶችን አጥቂው ተመቻችቶ የግብ ሙከራዎችን እንዳያደርግ በማድረጉ ረገድ የቡናማዎቹ ተከላካዮች ጥሩ የመጀመሪያ አጋማሽን አሳልፈዋል ።

እስከ 22ኛው ደቂቃ ድረስ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሳጥን ኳስ ይዘው ለመግባት ሳይቸሉ የቆዩት ቡናማዎቹ በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ ሃይለሚካኤል አደፍርስ በግራ የሳጥኑ አቅጣጫ ይዞ የገባውን ኳስ ለመስፍን ታፈሰ ለማቀበል ሞክሮ መስፍነ ሳይደርስበት ቀርቷል ።

መስፍን ታፈሰ በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይም ከሳጥን ውጪ ወደ ግብ የመታቸው ኳሶች ኢላማቸውን መጠበቅ አልቻሉም ነበር ።

ጨዋታው 31ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ ቀደም ባሉት ደቂቃዎች ላይ ከነበሩት የግብ ሙከራዎች ይበልጥ ለግብ የቀረበ ጠንካራ ሙከራ ታይቷል ። ቢንያም በላይ ከቀኝ መስመር አቅጣጫ ያሻገረውን ኳስ አቤል ያለው በግንባር ገጭቶ ወደ ግብ ያደረገውን የግብ ሙከራ በረከት አማረ በድንቅ ብቃት ግብ ከመሆን አድኖታል ።

በቀኝ መስመር ከአቤል ያለው ጋር በነበረው ጥምረት የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ሲጥር የነበረው ቢንያም በላይ በአጋማሹ የመጨረሻ አንድ ሶስተኛ ደቂቃዎች ላይ በግራ መስመር በኩል ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶች አድርጓል ።

በ41ኛው ደቂቃ ላይ ናትናኤል ዘለቀ ከሳጥን በቅርብ ርቀት ሆኖ ወደ ግብ ያደረገው ሙከራ ኢላማውን ሳይጠብቅ ቀርቷል ።

የጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽም ያለግብ ተጠናቋል ።

ከመጀመሪያው አጋማሽ በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ በታየበት እና በሁለቱም በኩል ግቦችን የተመለከትንበት የሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታው ውጤት የወሰኑ ሁነቶች አሳይቶን አልፏል ።

ቡናማዎቹ ብሩክ በየነ ወደ ኋላ በመሳብ ከቡድን አጋሮቹ ጋር በሚያደርጋቸው ቅብብሎሽ የቅዱስ ጊዮርጊስ የኋላ መስመርን በመስበር የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶች አድርገዋል ።

በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል በተለይም ከመስመር አና ከማዕዘን በሚነሱ የአየር ኳሶች ረጃጅም ተጫዎቻቸውን በመጠቀም የግብ ዕድሎች ለመፈጠር ጥረዋል ።

በ55ኛው ደቂቃ ላይ ከቀኝ መሰመር አቤል ያለው ያቀበለውን ኳስ ተጠቅሞ ናትናኤል ዘለቀ ወደ ግብ የመታውን ኳስ በረከት አማረ ግብ ከመሆን አግዶታል ።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ኢትዮጵያ ቡናዎች በፈጣን መልሶ ማጥቃት ይዘው የገቡትን ኳስ በመስፍን ታፈሰ እና ብሩክ በየነ አለመግባባት ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ።

የፈረሰኞቹ ጫና ይበልጥ አይሎ በታየባቸው ደቂቃዎች ላይ የአምና ሻምፕየኖቹ ቀዳሚ የሆኑበትን ግብ አግኝተዋል ። ቶጎአዊው እስማኤል ኦሮ አጎሮ ከጋቶች ፓኖም የተቀበለውን ኳስ በጠንካራው የግራ እግሩ አክርሮ በመምታት በ66ኛው ደቂቃ ላይ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

ግዙፉ አጥቂ ግቡን ማስቆጠሩን ተከትሎ በውድድር አመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 24 አድርሷል ።

ነገር ግን የቅዱስ ጊዮርጊሶች ደስታ መዝለቅ የቻለው ለስድስት ያህል ደቂቃዎች ነበር ። በ72ኛው ደቂቃ ላይ 10 ቁጥር ለባሹ ብሩከ በየነ ከአማኑኤል ዮሐንስ የደረሰውን አስደናቂ ኳስ በቅዱስ ጊዮርጊስ መረብ ላይ አሳርፏል ።

በቀጣዮቹ የጨዋታው ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ተጨማሪ ግብ አስቆጥረው ለመውጣት ፍላጎቶች የታዩባቸው የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ማሳየት የቻሉ ሲሆን በይበልጥ ግን ፈረሰኞቹ የተሻሉ ዕድሎችን መፍጠር ችለዋል ።

በተለይም ከማዕዘን በሚነሱ ኳሶች በኦሮ አጎሮ ፣ ፍሪምፖንግ ሜንሱህ እና ጋቶች ፓኖም የተደረጉ ሙከራዎች ተደርገው ነበር ፤ ምንም እንኳን ኢላማቸውን መጠበቅ የቻሉ ባይሆኑም ።

የቅዱስ ጊዮርጊሱን የግብ ዘብ የፈተኑ የግብ ሙከራዎችን ለማድረግ ያልቻሉት ቡናማዎቹ በተደጋጋሚ ወደ ተጋጣሚያቸው የግብ ክልል ለመድረስ ያደረጓቸው ጥረቶች ስኬታማ አልነበሩም ።

በመጨረሻም ጨዋታው በአንድ ለአንድ ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል ።

በ29ኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ሰኔ 24 ቅዳሜ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል እንዲሁም በተከታዩ ቀን ዕሁድ ሰኔ 25 ከ9:00 ጀምሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጨዋታውን ያደርጋል ።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የኢትዮጵያ አምባሳደሯ ኢንተ. አርቢትርሊዲያ ታፈሰ ከዳኝነቱ አለም ነገ በክብር ትሸኛለች…
Next Article የ28ኛ ሳምንት ቀሪ ጨዋታዎች ውሳኔ እና የጨዋታ ቦታ እና ሰዓት ማስተካከያ!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችሲዳማ ካፕ

ሲዳማ ካፕ ከመስከረም 16 እስከ 25 ይካሄዳል

Habtamu Mitku By Habtamu Mitku 4 years ago
“ጨዋታውን ከሜዳችን ውጪ ጨርሰን ለመምጣት እንሞክራለን” አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ “ስለምናልፍ የአስገዳጁ ነገር ችግር አይፈጥርብንም” አቶ ባህሩ ጥላሁን “ተጠያቂ የምናደርገው ራሳችንን ነው” ታሪኳ በርገና
አዳማ ከተማ አሰልጣኝ ዘርአይ ሙሉን ለመቅጠር ወሰነ
ደግፌ አለሙ የሶስት ጨዋታ እገዳ ሲጣልበት ኢትዮ ኤሌትሪክ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ እያንዳዳቸው የ አምስት ሺ ብር ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
የጨዋታ ዘገባ | ጅማ አባጅፋር ወሳኝ ድል ቀንቶታል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?