የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ጥር 10 2016 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በሳምንቱ መርሃግብር በተደረጉ ጨዋታዎች ስድስት በመሸናነፍ ቀሪ ሁለቱ በአቻ ውጤት ሲጠናቀቁ 20 ጎሎች በ19 ተጫዋቾች ተቆጥረዋል። 37 ቢጫ ካርድ ለተጫዋቾችና ቡድን አመራሮች ሲሰጥ ሶስት ቀይ ካርድ(በሁለተኛ ቢጫ) ተመዝግቧል ።
በሳምንቱ አምስት ተጫዋቾች እና አንድ አሰልጣኝ ላይ የዲሲፕሊን ውሳኔ ተላልፏል። ዓለምብርሀን ይግዛው(ፋሲል ከነማ)፣ ያሬድ ባየህ(ባህርዳር ከተማ) እና ያሬድ ካሳዬ(ኢትዮጵያ መድን ) በሳምንቱ ጨዋታዎች ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀማቸው ቀይ ካርድ አይተው ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ሲሆን ተጫዋቾቹ ለፈፀሙት ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገዱ እንዱሁም ጊት ጋትኩት(ሲዳማ ቡና) እና ቢንያም ፍቅሩ(ወላይታ ድቻ) በተለያዩ 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ የተመለከቱ ለፈፀሙት ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገዱና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍሉ ተወስኗል ።
አሰልጣኝ ዘማሪያም ወልደ ጊዮርጊስ (ሻሸመኔ ከተማ – ዋና አሰልጣኝ) ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር በነበረው የ10ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ግጥሚያው ከተጠናቀቀ በኋላ ለመገናኛ ብዙሃን አሰራርን የሚተች እና የጨዋታ አመራሮችን ክብር የሚነካ አስተያየት ስለመስጠታቸው ሪፖርት ቀርቦባቸው አሰልጣኙ ለፈፀሙት ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 3 /ሶስት ወር/ ጨዋታ እዲታገዱና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 10000 /አስር ሺህ/ እንዲከፍሉ ወስኗል::
በሁለት ክለቦች ላይም የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተላልፏል። ኢትዮጵያ መድን እና ባህርዳር ከተማ በሳምንቱ የየክለቦቻቸው አምስት ተጫዋቾች በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍሉ ተወስኗል።