*…. ባህርዳር ከተማዎች ደግሞ ነገ ወደ ሀገር ቤት
ይመለሳሉ ….
በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒየንስ ሊግ እየሳተፈ የነበረውና በአል አህሊ በደርሶ መልስ 7ለ0 ተሸንፈው ወደ ቀጣይ ዙር ማለፍ ያልቻሉት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ፊታቸውን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አዙረዋል።
ቅዱስ ጊዮርጊሶች ከካይሮ ግብጽ ባለፈው እሁድ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ የገቡ ሲሆን የፊታችን እሁድ መስከረም 27/2016 ከወልቂጤ ከተማ ጋር ላለባቸው የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታ በክቡር ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ልምምዳቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።
- ማሰታውቂያ -
በኮንፌዴሬሽን ካፕ እየተሳተፈ የነበረውና ወደ ምድብ ድልድል ሊገባ ከጫፍ ደርሶ በክለብ አፍሪካ 3 0 ተረትቶ በአጠቃላይ ውጤት 3 ለ2 ተሸንፎ ማለፍ ያልቻለው ባህርዳር ከተማም ከቱኒስ ቱኒዚያ ነገ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ የሚመለስ ሲሆን የፊታችን እሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ከኢትዮጵያ መድን ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።