መነሻ ገጽ Betaking Ethiopia Primer League ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 11ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !
Betaking Ethiopia Primer Leagueቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 11ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !

አጋራ
አጋራ

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 11ኛ ሳምንትና የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 11ኛ ሳምንት በተደረጉ ሰባት ጨዋታዎች አምስት ጨዋታዎች በመሸናነፍ ሁለት ጨዋታ በአቻ ሲጠናቀቁ 16 ጎሎች በ14 ተጫዋቾች ተቆጥረዋል። የጎሎቹ አገባብ ሁለት በፍፁም ቅጣት ምት ቀሪዎቹ በጨዋታ የተቆጠሩ ናቸው። በሳምንቱ 39 ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በቢጫ ካርድ ሲገሰፁ አንድ ተጫዋች በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ታህሳስ 01/2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በተጫዋች ተባረክ ሔፋሞ (ሃዋሳ ከተማ) ክለቡ ከ መቻል ጋር ባደረገው ጨዋታ በ77 ኛ ደቂቃ ላይ ከባድ የአጨዋወት ጥፋት ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል አቶ ጌታቸው ታዳሙ /የቡድን መሪ ወልቂጤ ከተማ / ክለቡ ከኢትዮጵያ መድን ጋር በነበረው የ11ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ ቅድመ ስብሰባ ወቅት ከ15 ደቂቃ በላይ ዘግይተው ስለመምጣታቸው ሪፖርት የቀረበባቸዋል ለፈፀሙት ጥፋት ከለቡ በፕሪምየር ሊጉ የውድድር ደንብ መሰረት የቡድን መሪው ብር 1000/አንድ ሺህ/ እንዲከፍሉ ወስኗል።

በክለቦች ሀዲያ ሆሳዕና በሳምንቱ ጨዋታ የክለቡ አምስት ተጫዋቾች በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል ሲወሰን ድሬዳዋ ከተማ ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር በነበረው የ 11ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የክለቡ ደጋፊዎች አፀያፊ ስደብ ስለመሳደባቸውና የተቃራኒ ቡድን ተጫዋች ላይ ቁሳቁስ ስለመወርወራቸው ሪፖርት ቀርቦበት በዕለቱና ከዚህ በፊት የከለቡ ደጋፊዎች ተሳድበው በተቀጡት ቅጣት ሊታረሙ ባለመቻላቸው በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ብር ሰባ አምስት ሺህ / 75000/ እንዲሁም የተቃራኒ ቡድን ተጫዋች ላይ ቁሳቁስ በመወርውራቸው ብር 25000 /ሃያ አምስት ሺህ/ በድምሩ ብር የ100000 /አንድ መቶ ሺህ/ እንዲከፍል ወስኗል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...