መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሰልጣኝ ተመስገን ዳና የኢትዮጵያ ቡና የስንብት ደብዳቤ አልቀበልም አለ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አሰልጣኝ ተመስገን ዳና የኢትዮጵያ ቡና የስንብት ደብዳቤ አልቀበልም አለ

አጋራ
አጋራ

ተሰናባቹ የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ክለቡ ያቀረበለትን በስምምነት እንለያይ ጥያቄ ውድቅ አደረገ።

ከደቂቃዎች በፊት አሰልጣኝ ተመስገን ዳና እንደተናገረው” ከኢትዮጵያ ቡና የቀረበልኝ በስምምነት የመለያየት ጥያቄን ብቀበለውም የስምምነቱ ይዘት ላይ ጥያቄ በማንሳት የስንብት ደብዳቤውን ሳልቀበል ወጥቻለሁ ውሉ ላይ ከመጀመሪያ ዙር 30 ጨዋታ 75 በመቶ ወይም ከ1-3 ማሳካት ይላል በ15ቱ ጨዋታ ላይ ባላሳካም ከ1-3 የሚለውን አሳካለሁ ብልም አልተቀበሉኝም እኔም በስምምነት የሚለውን ጥቅማ ጥቅሜና ደመወዜ ላይ ያለውን ባለመቀበሌ የሰጡኝን ደብዳቤ ሳልወስድ ወጥቻለሁ” ብሏል። አሰልጣኙ እንዳለው ” በውል መቋረጡ ላይ ፍቃደኛ ነኝ ነገር ግን በውሌ መሠረት ያለኝ ክፍያና ጥቅማ ጥቅም ዙሪያ ላይ ከጠበቃዬ ጋር ተነጋግሬ አሳውቃለሁ” ብሏል። አሰልጣኙ ግን ደብዳቤውን ተቀብሎ ምላሽ መስጠት እየቻለ አልቀበልም ማለቱ ለሌላ ውዝግብ በር እንዳይከፍት ስጋት ፈጥሯል።

በጉዳዩ ዙሪያ የተጠየቁት የክለቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ ግን ” በውላችን መሠረት አሰናብተነዋል። ውሉ ከጨዋታው 75 በመቶ ድል ማሳካት አለበለዚያ ከ1-3 መውጣት ከሚለው አንዱን ካላሳካ የማሰናበት መብት አለን ለዚህም ነው ያሰናበትነው” ሲሉ ገልጸዋል። ዋና ስራ አስኪያጁ እንደተናገሩት “በውሉ መሠረት ከሁለቱ ተዋዋዮች አንዱ ውል ማቋረጥ ከፈለገ ከአንድ ወር በፊት አሳውቆ ውሉን ማቋረጥ ይችላል ይላል እኛም በውላችን መሠረት ከታህሳስ 30/2015 ጀምሮ ውላችንን አቋርጠናል ብለን ነግረነዋል ደመወዙን ይከፈለዋል ቡድኑ ጋር መሄድ ግን አይችልም” በማለት የክለቡን አቋም አሳውቀዋል።

ኢትዮጵያ ቡና በሀድያ ሆሳዕና የደረሰበት የ1ለ0 ሽንፈት የአሰልጣኙን ስንብት ያረጋገጠ ሲሆን በያዘው 14 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ከአዳማ ከተማ ጋር አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው ከመሪዎቹ ቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ መድን በ8 ነጥብ አንሶ መገኘቱ አመራሮቹን ያበሳጨ ይመስላል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...