መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ተመስገን ዳናን በይፋ አሰናበተ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ኢትዮጵያ ቡና ተመስገን ዳናን በይፋ አሰናበተ

አጋራ
አጋራ

ኢትዮጵያ ቡና ውጤታማ አልሆነም በሚል ከአሰልጣኝ ተመስገን ዳና ጋር መለያየቱ ይፋ ሆኗል።

አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ቡድኑን ውጤታማ እንደሚያደርግ ቃል ቢገባም የተመዘገበው ውጤት በዝውውሩ ከፍተኛ ተሳትፎ ያደረጉትን የኢትዮጵያ ቡና አመራሮችን ያስደሰተ አልሆነም። በዘንድሮ የውድድር አመት ባደረጋቸው 10 ጨዋታዎች በአራቱ አሸንፎ በተመሳሳይ በአራቱ ተሸንፎ ሁለት ጨዋታ ብቻ አቻ የወጣው አሰልጣኙ በተለይ በሀድያ ሆሳዕና 1ለ0 መሸነፉ ለስንብቱ ትልቁን ሚና መጫወቱ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ቡና የዛሬ 12 ቀን ከአዳማ ከተማ ጋር ቀሪ ጨዋታውን የሚያደርግ ሲሆን በ12ኛው ሳምንት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ወደ አዳማ ከተማ በመዞሩ ከተስተካካይ ጨዋታው በኋላ በ13ኛ ሳምንት ከኢትዮጵያ መድን ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ በማከናወን ለቻን ውድድር ዝግጅት ውድድሩ ሲቋረጥ በቂ የማገገሚያ ጊዜ እንደሚኖረው ተገምቷል። ከድሬዳዋ ባገኘሁት መረጃ ደግሞ አሰልጣኙ ከክለቡ በመሰናበቱ ከክለቡ ሆቴል በመልቀቅ ወደ ኤርፖርቴት እየሄደ መሆኑ ታውቋል።

አመራሮቹ በቀጣዩ 11 ቀን አዲሱን አሰልጣኝ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የውጪ ሀገር አሰልጣኝና የአገር ውስጥ አሰልጣኞችን በማነጋገር ስራ ላይ መጠመዳቸውም እየተነገረ ነው።

በእስካሁኑ የአስረኛ ሳምንት ውጤት መሠረት ኢትዮጵያ ቡና በ14.ነጥብ በደረጃ ሰንጠረዡ 9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...