አዳማ ከተማ የዲሲፕሊን ጥሰት ፈጽመዋል ቡድኑን ጎድተዋል ያላቸውን ስድስት ተጨዋቾቹን መቅጣቱ ታወቀ።
ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ የዲሲፕሊን ጥሰት ፈጽመዋል የአቋም መውረድ አሳይተዋል የተባሉ ስድስት ተጨዋችቹ ላይ ከአንድ ወር ደመወዛቸው 80 በመቶ ቅጣት በማስተላለፍ ሁለት ተጨዋቾቹ ላይ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ታውቋል።
ክለቡ በርካታ ወጣቶችን ወደ ቡድኑ በመቀላቀል ለአዳማ ከተማው ፍልሚያ የተዘጋጀ ቢሆንም ቅጣት የተላለፈባቸው ተጨዋቾች ስነምግባር ጥሰት ወጣቶቹን እንዳያበላሽ ክትትል እንደሚያደርግና ቀጣይ ርምጃ እንደሚወስድ ከታማኝ ምንጭ የተገኘው መረጃ ያስረዳል። የስድስት ተጨዋቾቹን ማንነት ምንጫችን ከመግለጽ ቢቆጠብም በቀጣይ የተጫዋቾቹን ዝርዝር የምናሳውቅ ይሆናል።
በዲሲፕሊን ላይ አይደራደርም የሚባልለት አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ በ2014 ዲሲፕሊን ጥሰዋል በሚል ሁለት ተጨዋቾችን ከቡድኑ ማባረሩ ይታወሳል።
በአዳማ ከተሚ ለሚካሄደው ውድድር ዝግጅቱን እያደረገ ያለው አዳማ ከተማ በ14ኛ ሳምንት መርሃግብር ከኢትዮጵያ መድን ጋር ይገናኛል