አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በመግለጫቸው በሀገር ቤት ዝግጅት ከጀመሩ በኋላ ከጃንዋሪ 4 ጀምሮ ወደ ሞሮኮ ባምራት ዝግጅት ማድረጋቸውን እና ከሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ጋር ሁለት የዝግጅት ጨዋታዎች እንዳደረጉ ገልፀው ከትናንት በስቲያ ወደ አልጄርያ በመምጣት ለነገው ጨዋታ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል። መስኡድ መሀመድ በበኩሉ በሀገር ቤት እና በሞሮኮ ጥሩ የዝግጅት ጊዜ እንዳሳለፉ ገልፆ የሁሉም ተጫዋቾች ጤንነት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ለጨዋታው ዝግጁ መሆናቸውን ተናግሯል።
በአፍሪካ ዋንጫ ላይ የተካፈሉ ተጫዋቾችን በቻን ውድድርም ስለመጠቀም ተጠይቀው አሰልጣኝ ውበቱ በሰጡት ምላሽ ” የኛ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ሲካፈልም በአመዛኙ በሀገር ውስጥ በሚጫወቱ ተጫዋቸች በተገነባ ቡድን ነው። ያም ሆኖ በአፍሪካ ዋንጫ ከተቀምነው ቡድን ቋሚ ተሰላፊዎች አራቱ በጉዳት ምክንያት በዚህ ስብስብ አላካተትንም። ከዛ በተረፈ ተጫዋቾቻችን በውድድሩ ራሳቸውን ለማሳየት ዝግጁ ናቸው። ጥሩ የውድድር ጊዜ እናሳልፋለን ብዬ አስባለሁ።” ብለዋል።
አምበሉ መስኡድ መሐመድ ስለ አስተናጋጇ አልጄርያ እና ስለ ውድድሩ ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ ነው ” በአልጄርያ ያለው የልምምድ ፋሲሊቲ እና ሆቴል መስተንግዶ ጥሩ ነው። በአስተናጋጇ ሀገር ምድብ ውስጥ መሆን ትንሽ ይከብዳል። ሆኖም የመጀመርያ ጨዋታ ላይ ነው ትኩረት ማድረግ ያለብን። በጥሩ ሁኔታ ውድድሩን ከጀመርን በውድድሩ ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ እንችላለን።” ብሏል።
የሞዛምቢክ አሰልጣኝ ቺኪንዮ ኮንጄ እና የቡድኑ አምበል በተመሳሳይ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በአልጄርያ ቀድመው በመገኘት ዝጅግት እንዳደረጉ ገልፀው ከኢትዮጵያ ጋር የሚያደርጉት የመጀመርያ ጨዋታ ላይ ትኩረት አድርገው እንደሰሩ ተናግረዋል።
EFF