በኢትዮጵያ ፕርምየር ሊግ 12 ሳምንት መርሀግብር በደረጃ ግርጌ ላይ የሚገኝው አርባምንጭ ከተማ በሜዳው በደረጃ ሰንጠረዡ 4 ደረጃ ላይ የሚገኝውን አዳማ ከተማን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች የሚያደርጉት ጨዋታ በሳንምንቱ ተጠባቂ ከሚባሉ ጨዋታዎች መካከል አንዱ ስሆን፡፡
አርባምንጭ ከተማ ካለበት የውጤት ቀውስ እና ተደጋጋሚ ሽንፈት ለመወጣት ይህንን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ ሚገባ ሲሆን፡፡
አዳማ ከተማም ቢሆን እንዳለፉት አመታት በዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመግባት ከዚህም ጨዋታ ሶስት ነጥብ ማሳካት ግድ ይለዋል፡፡
በነገው ጨዋታ በሁለቱም በኩል የሚደረጉ ፈጣን እንቅስቃሴወችን የምንመለከት ሲሆን በመሀል ክፍል ተጫዋቾች መካከል ኳስን ብልጫ ወስዶ ለመጫወት የሚደረገውን ሽኩቻ ሰፊ ያደርገዋል፡፡ አሰልጣኝ እዮብ ማሌ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በሚያደርጉበት ጨዋታ ቡድን ከገባበት የውጤት ቀውስ ለማውጣት ስፓርት ወዳዱ የከተማው ህዝብ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡
- ማሰታውቂያ -
በአርባምንጭ ከተማ በኩል አሌክስ አሙዙ፣ ላኪ ሳኒ፣ ብርሀኑ አዳሙ፣ ወንደሰን ሚልኪያስ በጉዳት ለጨዋታው ማይደርሱ ሲሆን ታድዮስ ወልዴ፣ተካልኝ ደጀኔ ፣ፀጋዬ አበራ ከጉዳታቸው በማገገም ወደ ሜዳ ይመለሳሉ፡፡
ሱራፌል ዳኛቸው፣ ሱሌማን መሀመድ፣ አዲስ ህንፃ እና ሚካኤል ጆርጅ በአዳማ ከተማ በኩል ጉዳት ላይ ያሉ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች አምና በአርባምንጭ ስታድየም ተገናኝተው 0-0 በሆነ የአቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡