አሁንም እንደ በፊቱ ቀጠሮ ላይ ቀልድ አናውቅም ከተባሉ ያለጥርጥር አባባሉ የሃትሪክ ነው….
እንዳልነው ነገ ጠዋት በቀጠሮው ሰአት እንገኛለን
*… ስለ ኢትዮጲያዊው ኮሊና ያውቃሉ? የመሃል ሜዳ አለቃ ሆኖ ለ 23 አመታት በመሃል ዳኝነቱ የሚታወቀው ኢትዮጲያዊው ኮሊና ኪነ ጥበቡ በነዚያ ዘመናት የሚጸጽተኝ ስራ አልሰራሁም ሲል ይናገራል…ነገ ጠዋት ሀትሪክ ላይ ይጠብቁት….
*…በኢትዮጲያ ቡና መሀል ክፍል እየፈነጨ ያለው ወጣቱ ዊሊያም ሰለሞን/ኢትዮጵያዊው ዊሊያም ሼክስፒር/ ጅማ አባጅፋር ላይ ያስቆጠረውን ግብ መታሰቢያነት ለእናቱ ሰጥቷል….. ለዋሊያዎቹም ዝግጁ ነኝ ሲል አሰልጣኝ ውበቱ አባተን ያሳስባል….
*…የቅዱስ ጊዮርጊሱ የኋላ ደጀን አስቻለሁ ታመነ ለቅዱስ ጊዮርጊስ እያንዳንዱ ጨዋታ የዋንጫ ያህል ነው ይላል……
- ማሰታውቂያ -
*…ጅማ ላይ በነበሩት የዋሊያዎቹ ዝግጅት ላይ ከቀሩት የጊዮርጊስ ተጨዋቾች ውጪ አርፍደው በመድረሳቸው ተመለሱ የተባሉት ሁለቱ ተጨዋቾች ማናቸው? ሃትሪክ ደርሳበታለች ነገ ይጠብቋት…..
*….ከከፍተኛ ሊግ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያደጉት ዳኞች በብቃት ሳይሆን በኮታ ነው መባሉን ብሄራዊ የዳኞች ኮሚቴ አስተባብሏል….
ከውጪ ደግሞ፦
*….በማን.ዩናይትድ ዳግም የገነነው ፖል ፖግባ ዙሪያ መረጃ ይዘናል….
*…ስለ እግርኳስ ውበት ሜሱት ኦዚል ስንብት የምንሎት ነገር አለ…..
*…እንደ አዲስ ስለተወለደው ዕድሜ ጠገቡ ዝላታን ኢብራሂሞቪች መረጃም ተኳቷል…
*…የመድፈኞቹ የለውጥ ሀዋርያ ኢሚል ስሚዝ ሮው የተዘጋጀ ዘገባም ይዘናል….
ነገ ጠዋት ሀትሪክ እጅዎ ስትገባ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች አዳዲስና ያልተሰሙ መረጃዎችን ያገኛሉ
ነገ ጠዋት ሀትሪክን በእጅዎ ቢያስገቡ ይጠቀማሉ ይዝናናሉ
……ቅዳሜና እሁድዎ የተባረክ ይሁን…….