ነሐሴ 28 ከጋና ጋር የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዉን የሚከዉነዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዚያ አስቀድሞ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን እንደሚያደርግ ይታወቃል።
ከአለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታዎች በፊት የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታውን በዛሬዉ ዕለት ከሴራሊዮን ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚያደርግ ሲሆን ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታውን ደግሞ ከዩጋንዳ በሔራዊ ቡድን ጋር ነሀሴ 23/2013 ዓ.ም በባህርዳር አለም አቀፍ ስታዲየም የሚያካሂድ ይሆናል።
በዚህም መሰረት ከዋልያዎቹ ጋር በዕለተ እሁድ የወዳጅነት ጨዋታውን የሚያደርገዉ የኡጋንዳ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታው ወደ ሚደረግበት ባህርዳር መድረሱ ታዉቋል።