By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ለኮሎምቢያው የዓለም ዋንጫ ለማለፍ 180 ደቂቃ የቀረው የሴቶች ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ለወሳኝ ፍልሚያ ወደሞሮኮ አቅንቷል….
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችU 20 ሴቶች

ለኮሎምቢያው የዓለም ዋንጫ ለማለፍ 180 ደቂቃ የቀረው የሴቶች ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ለወሳኝ ፍልሚያ ወደሞሮኮ አቅንቷል….

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
Share
SHARE

“የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተጣራ 120 ሺህ ብር ደመወዝና የሁለት ዓመት ኮንትራት ቢፈቅድልኝም ተፈጻሚ ሳይሆን ግን ሁለት ወር አልፎኛል”

አሰልጣኝ ፍሬው ኃ/ገብርኤል
/ከ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ/

‘”የቀረበለትን ውል አልቀበልም ያለው አሰልጣኙ ራሱ ነው”

አቶ ባህሩ ጥላሁን
/ የኢት.እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ /

- ማሰታውቂያ -

“ለወሳኙ ፍልሚያ የምንሄደው ሰው ሜዳ ነው ይሄ ቡድን ደግሞ በሰው ሜዳ አሸንፎ መምጣት የሚችል መሆኑን አሳይቷል” ሲሉ የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ፍሬው ኃ/ገብርኤል ተናገሩ።

 

አሰልጣኙ የፊታችን ቅዳሜ ከሞሮኮ አቻቸው ጋር ባለው ወሳኝ የማጣሪያ ጨዋታ ዙሪያ ዛሬ በፌዴሬሽኑ አዳራሽ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ” ቡድኑ ባለፉት 23 ቀናት ሲዘጋጅ ቆይቷል 31 ተጨዋቾች ጠርተን 23 በማስቀረትና አዳዲስ ፊት በማምጣት ስንዘጋጅ ቆይተናል ከ23ቱ ተጨዋቾች አንድ ተጨዋች ብቻ በፓስፖርት ምክንያት በመቅረቷ 22 ተጨዋቾችን በመያዝ 35 ሜዳ እና በአዲስ አበባ ስታዲየም ልምዳችን ስንሰራ ቆይተናል። በዚህ አጋጣሚ ሁለቱንም ሜዳ የፈቀዱልንና አካላት እናመሰግናለን አዲስ አበባ ስታዲየምን የፈቀዱልን የባህሕልና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ የሆኑትን አምባሳደር መስፍን ቸርነትን አመሰግናለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ጥሩ ዝግጅት ብናደርግም ሙያዬ በሚፈቅደው ደረጃ ግን አይደለም ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን ጠይቄያለሁ
ሞሮኮ ከሰባት ቀን በፊት አስቀድመን ሄደን እንዘጋጅ ብዬ ነበር ሁለቱም አልሆነም ከአንድ ወንድ ቡድን ጋር ብቻ ነው የተጫወትነው የምንሄደውም ከሶስት ቀን በፊት ነው ….ፕላን ኤ ቢቀር ፕላን ቢ ብለን ተዘጋጅተን የመጨረሻውን ልምምድ አድርገን ዛሬ ወደ ሞሮኮ እናቀናለን ሞሮኮ ግን በ10 ቀን ውስጥ ከአልጄሪያና ቦትስዋና ጋር ተጫውታና ተዘጋጅታ ነው የምትገጥመን..” ያሉት አሰልጣኙ ” ያም ቢሆንም የምንሄደው ሰው ሜዳ ነው ይሄ ቡድን ደግሞ በሰው ሜዳም ቢሆን አሸንፎ መምጣት የሚችል መሆኑን አሳይቷል” ሲሉ አስረድተዋል።

ስለ አራት አመት ቆይታቸው የተናገሩት አሰልጣኝ ፍሬው “በቆይታዬ ከ31 ተጨዋቾች በላይ አምጥቻለሁ በሀሳብ የሚጫወት ቡድንም እንዲገነባ ትልቅ ስራ ሰርቻለሁ በናይጄሪያ ጨዋታ ከነበሩ 11 በጋና ጨዋታ ከነበሩ መሃል 7 ተጨዋቾች ተካተዋል በስራዬ ለዋናው ብሄራዊ ቡድን የብዙ አመት ግልጋሎት የሚሰጡ ተጨዋቾችን በማፍራቴ የልማት ስራ እንደሰራሁና ሀገሬን የምጠቅምበት እድል እንደፈጠርኩ ይሰማኛል በዚህ ምክንያት በእራት አመት ቆይታዬ ደስተኛ እንድሆን አድርጎኛል” ሲሉ ሂደቱን አብራርተዋል።

አሰልጣኙ ውላቸው ከተጠናቀቀ በኋላ ሳይታደስ ዛሬ 20 ቀናት አልፏቸዋል በዚህ ዙሪያ ምን ምላሽ እንዳላቸው የተጠየቁት አሰልጣኙ “ውሌን ከጨረስኩ ወደ 16 ወይም 18 ቀናት አልፎኛል በኔ በኩል ማቅረብ ያለብኝን አቅርቤያለሁ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የተጣራ 120 ሺህ ብር ደመወዝና የሁለት አመት ውል ፈቅዶልኝ ወጥቻለሁ ተፈጻሚ ሳይሆን ግን ወራቶች አልፎኛል በኔ በኩል ውል አልፈረምኩም ብዬ ትቼ ግን አልወጣም ሀገሬን፣ ተጨዋቾቼንና ሙያዬን አከብራለሁ የተቀጠርኩት ከ20 አመት በታች ቡድን እንደመሆኑ መገምገም ካለብኝ በዚህ ቡድን ውጤት ብቻ ነው ተቋሙም ሙያዬን ሀገሬን ተጨዋቾቼን አስቦ ኮንትራቴን እንደሚሰጠኝ እጠብቃለሁ አሁንም ሀገሬን አስቀድሜለሁ ለኔ ፊርማ ሁለተኛ ጉዳይ ነው በቀጣይ የማወጣቸው ብዙ ነገሮች ሊኖሩ ግን ይችላሉ” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የስነ ምግብ ባለሙያው ድንገት ቡድኑን ትተው ስለመሄዳቸው የተጠየቁት አሰልጣኙ ” የስነምግብ ባለሙያው ማን እንዳመጣውም ለምን እንደቀረም አላውቅም ያመጣው ወገን ቢጠየቅ ይሻላል” ሲሉ አጠር ያለ ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህን የአሰልጣኝ ፍሬው ኃ/ገብርኤል መግለጫ ተከትሎ ጥያቄ የቀረበላቸው የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ባህሩ ጥላሁን ግን የአሰልጣኙን ሃሳብ አስተባብለዋል። ከስነ ምግብ ባለሙያው ጋር ተያይዞ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ባህሩ ” ቡድኑ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ይገኛል ሙሉ ድጋፍ እያደረግን ነው የስነ ምግብ ባለሙያው አስፈላጊነትም ሳይታለም የተፈታ ነው ስናመጣቸውም ከአሰልጣኙ ጋር ቁጭ ብለን ተነጋግረንበት መመሪያያ ተሰጥቶ ነው ወደ ስራ የገቡት … ከምግብ አቅርቦቱ ጋር ተያይዞ የተጨዋቾቹ አቀባበል ጋር ክፍተት ስለነበርና አሰልጣኙም የምጠብቀውን ድጋፍ አላደረጉልኝም ብለው ነግረውን ቡድኑን ተለይተው እንደወጡ እናውቃለን ” ሲሉ ተናግረዋል።

ከኮንትራቱ ጋር ተያይዞ ዋና ስራ አስፈጻሚው በሰጡት ምላሽ ” ነሀሴ 30/2015 በአሰልጣኙ ውል ዙሪያ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ቁጭ ብሎ ከተነጋገረ በኋላ ለሉሲዎቹ ሃላፊነት የሁለት አመት ኮንትራትና 120ሺህ የተጣራ ደመወዝ እንዲሰጣቸው ይወስናል ስራ አስፈጻሚው የወሰነውንና ያስቀመጠውን አካሄድ በመንተራስ ለአሰልጣኙ ለሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን የማሳለፍ ግዴታ ያለው የሁለት አመት ውልና የ120 ሺህ ብር የተጣራ ደመወዝ የተካተተበት ውል ቀርቦላቸው አልፈልግም አልፈርምም በማለታቸው ሳንስማማ ቀርተናል” ሲሉ ተናግረዋል።

” አሰልጣኙ አለመስማማታቸውን በማየት ፌዴሬሽኑም ታህሳስ 8/2016 ድረስ ባለው በ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን የሃላፊነት ውል እንዲቀጥሉ ይደረጋል.. ከዚያም ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ድጋሚ ይቀመጥና በ20 አመት በታች ቡድን ሃላፊነታቸው ለተጨማሪ አንድ አመት ኮንትራታቸው ታድሶ በ70 ሺህ ብር ደመወዝ እንዲቀጥሉ ይወስናል ይህን ለማስፈጸም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ዳኛቸው ንግሩና እኔ አሰልጣኙን እንድናናግር ተወሰነ ” ያሉት አቶ ባህሩ ” አሰልጣኙን ጠርተን በውሉ ዙሪያ ስናወራ የአንድ አመቱን ውል አልቀበልም” ሲሉ መልሰዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከፕሬዝዳንቱ አቶ ኢሳያስ ጅራ ጋር የተነጋገሩ ሲሆን በኮንትራቴ ዙሪያ ከሞሮኮ ጨዋታ መልስ በድጋሚ እናወራለን እስከዚያ ድረስ በውሌ ዙሪያ ምንም አላወራም ብለው መውጣታቸውን ነው የምናውቀው ” ሲሉ አስረድተዋል። አቶ ባህሩ እንደሚሉት የአሰልጣኙ ውል ተጠናቆ ባይታደስም በነባሩ የ50ሺህ ብር ደመወዝ ስራቸውን እየሰሩ እንደሆነ ነው የምናውቀው ” ሲሉም አብራርተዋል።

አሰልጣኙ ያቀረቡት ሁለት ኢንተርናሽናል የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች ይዘጋጅልኝ ጥያቄ ለምን ተግባራዊ አልተደረገም የተባሉት አቶ ባህሩ ” የአሰልጣኙ የሁለት ኢንተርናሽናል የአቋም መለኪያ ጨዋታ ጥያቄን ተከትሎ ከፍተኛ ጥረት አድርገናል። በተለይ የኬንያና የቡሩንዲ አቻዎችን ለማግኘት ከፍተኛ ሙከራ አድርገን አልተሳካም በተለይ የዕድሜ ብሄራዊ ቡድኖችን ለአቋም መለኪያ ማግኘት ከሌሎቹ በላይ ይከብዳል በእኛ በኩል የምንችለውን ሞክረናል ግን አልተሳካም በቀጣይ የምንችለውንና የተለመደውን ድጋፍ ማድረጋችን ይቀጥላል” ሲሉ ለአሰልጣኝ ፍሬው ኃ/ገብርኤል አስተያየት ምላሽ ሰጥተዋል።

በላቲን አሜሪካዋ ሀገር ኮሎምቢያ ለሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ለማለፍ የ180 ደቂቃ ፍልሚያ የቀረው ከ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ደኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት ፣ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራና የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት በስካይላይት ሆቴል የምሳ ግብዣና ደማቅ አሸኛኘት የተደረገለት ሲሆን የፊታችን ቅዳሜ ከሞሮኮ አቻቸው ጋር ላለባቸው ጨዋታ ዛሬ ምሽት ወደ ሞሮኮ አቅንተዋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የወልቂጤ ከተማ የቡድን አባላት የጠፋ ንብረት ተገኘ
Next Article የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንና ኢትዮ ቴሌኮም ተጣመሩ….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችስሁል ሽረ

ስሑል ሽረ ግዙፉን ተከላካይ አስፈርሟል

ሚሊዮን ኃይሌ By ሚሊዮን ኃይሌ 6 years ago
የዋልያዎቹ የመጀመሪያ ተጋጣሚ ዝግጅት ጀምሯል
ኢትዮጵያ ቡናና አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ተጣምረዋል
ዲሲፕሊን ኮሚቴ ወልቂጤ ከተማን ቀጥቷል
ሀዋሳ ከተማ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች አስፈርሟል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?