ኢትዮ.ኤሌክትሪክ ለቀጣዮቹ ሁለት አመታት ክለቡን ይዞ እንዲቀጥል በቃል ደረጃ ከተስማማው አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ጋር ዛሬ ሊፈራረም መሆኑ ተሰማ።
ከክለቡ ታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ ከቀኑ 10 ሰአት በሀያት ሪንጀንሲ በሚካሄደው የፊርማ ስነስርዓት ላይ የአሰልጣኙ ኮንትራት ህጋዊነት ይረጋገጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ከከፍተኛ ሊግ ያደገው ኢትዮ.ኤሌክትሪክ ለዝውውር የመደበው በጀት አነስተኛ በመሆኑ አሰልጣኙ የሚፈልጋቸውን ተጨዋቾች የማግኘት ዕድሉን እንዳያበላሽበት ተሰግቷል። የክለቡ ቦርድ በጀቱ በሚስተካከልበት ሂደት ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎይጠበቃል።