By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ፈረሰኞቹ በፋይናንስ ራሳቸውን የማጠናከር ዘመቻ ሊከፍቱ ነው
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

ፈረሰኞቹ በፋይናንስ ራሳቸውን የማጠናከር ዘመቻ ሊከፍቱ ነው

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
Share
SHARE

“የሜድሮክ ግሩፕ ተቋማት ያልከፈሉን ወደ 67 ሚሊዮን ብር አለን አሁንም ታግሰን ክፍያውን እንዲሰጡን እየጣርን ነው “

” 8 አመት ሙሉ ተካሰናል ከአስራ አምስት ጊዜ በላይ ፍርድ ቤት ቀርበናል ሁሉንም ግን ረተናቸዋል”

አቶ ዳዊት ውብሸት
/ የቅ/ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር የቦርድ አባል/

ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሁለት አመታት የገጠመውን ከፍተኛ የፋይናንስ ችግር ለማስወገድ ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

- ማሰታውቂያ -

“የድርሻዬን ለታላቁ ቅዱስ ጊዮርጊስ” በሚል የፊታችን ቅድሜ በሚጀመረው የስጦታና የድጋፍ የኦንላይን ዘመቻ ዙሪያ በክለቡ ጽ/ቤት በተሰጠው መግለጫ ላይ የክለቡ የቦርድ አባልና የአስተባባሪ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ዳዊት ውብሸት እንደተናገሩት ” እውነት ነው ከፍተኛ የበጀት ችግር ተከስቶብናል አሉ የተባሉ ክለባችንን ያግዛሉ ብለን ያሰብነውን ስፖንሰሮች ጠይቀን በተወሰነ ፐርሰንት አልተሳካልንም። ስፖንሰሮቹ ኳሳችንን ወደው እስኪመጡ ድረስ ደጋፊዎቻችንን እናምናለን ጠንክረን እንደምንቀጥል ተስፋ እናደርጋለን” ሲሉ ተናግረዋል።

ኮሚቴው ከነሀሴ 20 እስከ ጳጉሜ 4/2015 ድረስ ቅዳሜ በሚገለጹ የክለቡ የባንክ አካውንቶች፣ በአለም አቀፍ የገቢ መለኪያ ስልቶችና በቴሌ ብር የገቢ ማሰባሰቢያ ስልት ከ5-10 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማድረግ እንደታቀደ ተገልጿል። ከ100 ብር ጀምሮ በተቀመጡት የአካውንት ቁጥሮች ሁሉም ድጋፉን እንዲያደርግ ተጠይቋል። በቅዳሜ መክፈቻ ከቀኑ 6 ሰአት ተጀምሮ ከለሊቱ 6 ሰአት ድረስ በክለቡ ሁሉም ማህበራዊ ፔጆችና 1ሚሊዮን ተከታዮች ባሉት በአባይ ቲቪ የፌስቡክ ገጽ ላይ ይተላለፋል ተብሏል። ክለቡንም ለማጠናከር አመታዊ 150 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋልም ተብሏል። ቡድኑ በቀጣዩ አመት ሻምፒዮናነቱን እንዲያስጠብቅ ለማድረግ የተጨዋቾች ዝውውር ላይ ጠንካራ ስራ ለመስራት እንደተዘጋጁም ገልጸዋል።

ታሪካዊ የክለቡ ተወዳጅ ተጨዋቾች ማሊየዎች ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን የስመጥር የቀድሞ ተጨዋቾች ማሊያዎች ለጨረታ ይቀርባሉ ተብሏል። አንድ ግለሰብ የክቡር ይድነቃቸው ማሊያና የጌታቸው ዱላ ቤተሰብ ደግሞ ማሊያውን ሰጥተውናል ደጋፊዎቹም ክለቡን የሚጠቅምና ታሪካዊ ነው ያላችሁት ማሊያ ሜዳሊያና ቁሳቁስ ለክለባችን እንድትሰጡን እንጠይቃለን ብሏል ኮሚቴው።

በክለቡ ጽ/ቤት በተሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ” በ87 አመት የክለባችን በድል የታጀበ ጉዞ ለሀገራችን ትልቅ ስራ ሰርተናል። ደጋፊዎቻችን፣ ለሀገራችን እግር ኳስ
ጥቅም እንደነበረን ለሚያምኑ የስፖርት ቤተሰቦች ጥሪ እናደርጋለን የመፍረስ ችግር ለገጠማቸው ክለቦች ደርሰናል አሁን ደግሞ እኛ ድጋፍ እንጠይቃለን እንደ ሀገራችን እግርኳስ ራሳችንን መሸጥ አልቻለም አለም ላይ እንዳለው ኢንዱስትሪ አይደለም ለዚህ ነው ስፖንሰር ያጣነው። እስካሁን ሲደግፉን እንጂ በኛ ተጠቅመው ነው ብለን አናስብም ራሳችንን ሸጠን ውጤታማ እስክንሆን ድረስ ድጋፍ እንጠይቃለን” ብለዋል አስተባባሪው።

በተፈጠረው የፋይናንስ ችግር ዙሪያ አቶ ዳዊት ሲናገሩ “ከዚህ በፊት በነበረው የረጅም አመት የቅ/ጊዮርጊስ ታሪክ ውስጥ በተለይ ከ1982 ጀምሮ የሜድሮክ ግሩፖች ፔፕሲ፣ ደርባንና ዳሽን ባንክን ጨምሮ ወደ 13 የሚጠጉ ተቋማት ሲያግዙን ኖረዋል። ባለፉት ሁለት አመታት ግን አትክፈሉ የሚል ትዕዛዝ ደርሶናል በሚል ክፍያውን በማቆማቸው ችግር ውስጥ ገብተናል። ከ7-10 አመት የሚጠጋ ውል አለን የተፈጠረው ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ታግሰናል።ተቋማቱ ያልከፈሉን ወደ 67 ሚሊዮን ብር አለን አሁንም ታግሰን ክፍያው እንዱሰጠን እየጣርን ነው ለሚድሮክ ግሩፕ ተቋማት
ከ8 ጊዜ በላይ በደብዳቤ ጠይቀን ምላሽ የለም” ሲሉ ተናግረዋል።

ከሜዳ ችግር ዙሪያ እንደተገለፀው ” እውነት ነው ሜዳ ቸግሮናል ያንን ሜዳ ለማሰራት ሜድሮክ ወደ 400 ሚሊዮን ብር በጅቶ ቢንቀሳቀስም አልተሳካም በአሁኑ ወቅት 1.2 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ይህንን ማድረግ ግን አልቻልንም ከዚህም በላይ የሊጉ ውድድር ተዟዙሪ ቢሆን ኖሮ ከ30 ጨዋታ በ 15ቱ የሜዳ ገቢ ይኖረን ነበር በአሁኑ ፎርማት የሆቴልና ሌሎች ወጪዎች ከፍተኛ ሆኖብናል ተጨዋቾቻችንን በዲሲፕሊን ደረጃ መቆጣጠር አልቻልንም” ያሉት አቶ ዳዊት በተለይ ክለቡን ለቅቀው ስለወጡ ተጨዋቾች እንደገለጹት ” ተጨዋቾቹ ክለባችንን ለቅቀው የወጡት በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በእኛም በኩል ውል ማደስ ስለማንፈልግ ነው አጎሮ ለተሻለ ለውጥ ተጓዘ ቻርለስን ስላልፈለግነው ውል አላደሰም በዝውውር ላይም መጣን ብለንው የቀሩ ተጨዋቾች አሉ ከውጪ ሞክረን እንመጣለን ብለው ሳይመጡ የቀሩ አሉ እውነቱ ይህ ነው
ከውጪ ተጨዋች አመጣችሁ ለተባለው ኮታ ስላለ ከ3ቱ ውጪ አላመጣንም ምክንያቱ ደግሞ በአፍሪካ ደረጃ ያለው ውድድራችንን ከፍ ለማድረግ ነው በሀገር ውስጥ ለሚካሄደው ውድድር የኛ ሀገር ተጨዋቾች በቂ ናቸው ከክፍያ ጋር ተያይዞ የተጋነነ ክፍያ አለ ብለን አናምንም
በኛ በኩል ሶስት አይነት የደመወዝ ክፍያ መንገድ አለን 1ኛ ደረጃ ሲኒየር ለሆኑና ኮከብ ለሆኑ 2ኛ ደረጃ ሲኒየር ተጨዋች ሆነው ከክለቡ ጋር የቆዩ የመጨረሻው 3ኛ ደረጃ ከቢ ቡድን ያደጉ ብለን እንደየደረጃቸው እንከፍላለን” ሲሉ አስረድተዋል።

ከፋይናንሺያል ፌርፕሌይ ህግ ጋር ተያይዞ የተጠየቁት አቶ ዳዊት ” እውነት ነው ህጉ ይኑር ብለን ለአመታት ጨቅጭቀን መልስ አጥተን ኖረናል ዘንድሮ በሊጉ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ባሉት ክለቦች መሃል ያለው ልዩነት 300ሺህ ብር አይሞላም በ1ኛና በ16 ኛ ደረጃ ባሉ ክለቦች መሃል ያለው የገቢ ልዩነት 3 ሚሊዮን ብር ብቻ ነው ልዩነቱ ማነሱ ልክ አለመሆኑን ነግረናል ጥሩው ነገር ከፋይናንሺያል ፌርፕሌይ ህግ አንጻር ምላሽ አግኝተን ህጉ እየተጠና ስለሆነ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ያሳውቃሉ ብዬ አምናለሁ” ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ዳዊት ያለፉት አመታትን የማርኬቲንግ ጥረታቸውና ውጤቱን ሲያብራሩ ” ከኮቪድ በፊትኮ በአመት ሶስቴ ለገና፣ ለፋሲካና ለእንቁጣጣሽ ባዛር እናዘጋጅና በየአመቱ 17 ሚሊዮን ገቢ እናገኝ ነበር በጊዜውም ጥሩ ስራ ሰርተናል አርፈንም አልተቀመጥንም ነበር 1000 ማሊያ በሶስት ሰዓት የሸጥንበት ጊዜም ነበር” ሲሉ ተናግረዋል።

ከክለቡ ጋር የነበሩ በተፈጠረ ልዩነት ክለቡን የለቀቁ ፍርድ ቤት ድረስ ድረስ የተካሰሱት ደጋፊዎች ዙሪያ በሰጡት ቁጣ የተሞላበት ምላሽ ” 8 አመት ሙሉ ተካሰናል ከአስራ አምስት ጊዜ በላይ ፍርድ ቤት ቀርበናል ሁሉንም ግን ረተናቸዋል። ክሳቸው ጠቅላላ ጉባኤ አልተጠራም ነው በጎን ጉባኤው እንዳይጠራ የሚያደርጉት እነሱ ናቸው የግል ጥላቻ ክለባችን ላይ አይሰራም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከማንም በላይ ነው ጉዳዩን ከስሩ ገብታችሁ ብታዩት የግለሰብ ጸብ ነው አንድም ቦታ ቅዱስ ጊዮርጊስ የለበትም ባለብኝ ሃላፊነት የክለቡን መብት ለማስከበር የምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ” ሲሉ አቶ ዳዊት ውብሸት ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ ዳዊት በሰጡት ማጠቃለያ “ለ15 ቀናት በሚደረገው ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ የሚዲያ አጋር ለመሆን የተስማማው ዓባይ ቲቪን እናመሰግናለን 1 ሚሊዮን ተከታይ ባለው የፌስቡክ ፔጁና ሌሎች መንገዶች ከኛ ጋር ሊሰራ በመዘጋጀቱ ተደስተናል በክለባችን ማህበረሰብ ስምም እናመሰግናለን” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ” የስታዲየሙ ዕድሳት ተጠናቆ በቀጣዩ አመት ፕሪሚየር ሊጉ ወደ አዲስአበባ ይመለሳል ” ዶ/ር ወገኔ ዋልታንጉስ /የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ የውድድር እና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ሰብሳቢ/
Next Article ፊፋ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሶስት ክለቦችን ከዝውውር አገደ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

ቅዱስ ጊዮርጊስና ጸሃይ ባንክ በጋራ ለመስራት ተስማሙ….

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
አለልኝ አዘነ ቅጣት ተላለፈበት
የቅዱስ ጊዮርጊስ ማልያ የድል ማልያ ነው ይሄን ማልያ መልበስ የአሸናፊነት ስሜት መላበስ ነው !! ሀብታሙ ጉልላት
አውስኮድ እግር ኳስ ቡድን መሪውን በሞት አጣ!
የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ እና ባህርዳር ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?