በዘንድሮዉ አመት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 42 ነጥቦችን በመሰብሰብ አስራ አንደኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቅ የቻለዉ ሲዳማ ቡና በዝውውር ገበያዉ ላይ በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ በመቀላቀል ላይ ሲገኝ አሁን ደግሞ ተጨማሪ ተጫዋች ወደ ስብስቡ መቀላቀሉ ተሰምቷል።
በዚህም የቀድሞዉ የፋሲል ከነማ ፣ ወልቂጤ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም የውድድር አመቱን አጋማሽ በኢትዮ ኤሌትሪክ ቤት ማሳለፍ የቻለዉ የመስመር አጥቂዉ አብዱራህማን ሙባረክ /ግሪዳዉ/ በሁለት አመት የኮንትራት ጊዜ የአሰልጣኝ ስዩም ከበደን ቡድን ሲዳማ ቡና መቀላቀሉ ታውቋል።