በዚህ የዉድድር አመት ለሲዳማ ቡና እንዲሁም ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጥሩ ግልጋሎት ሲሰጥ የነበረዉ እንዲሁም ያለፉትን ሁለት አመታት በሲዳማ ቡና ያሳለፈዉ ጊት ጋት በይፋ ኮንትራቱን አራዝሟል፤ቁመተ ረጂሙ ተከላካይ ሁለት አመታትን በሲዳማ ቡና የሚቆይ ይሆናል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሲዳማ ቡና ከብዙ ተጫዋቾች ጋር ስሙ የተያያዘ ሲሆን በመጪዉ ቀናትም ሌሎች አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ እንደሚቀላቅል ይጠበቃል።