በአሰልጣኝ ስዩም ከበደ እየተመራ በዝዉዉር መስኮቱ ላይ በንቃት በመሳተፍ ላይ እና እንዲሁም የነባር ተጫዋቾቹን ዉል በማደስ ላይ የሚገኘዉ ሲዳማ ቡና የወሳኝ አጥቂዉን ዉል ሲያራዝም እንዲሁም የግራ መስመር ተከላካይ አስፈርሟል።
የ2014 ዓ/ም የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከፍተኛ ጎል አግቢ ሆኖ ያጠናቀቀዉ እና የሲዳማ ቡና የተስፋ ቡድን ፍሬ የሆነዉ እና ለ6 ዓመት ክለቡን ያገለገለዉን ይገዙ ቦጋለን ሲዳማ ቡና ለተጨማሪ 2 ዓመት ዉሉን አድሷል።
- ማሰታውቂያ -
እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ የተስፋ ፍሬ በመሆን ዋናዉን ቡድን ለበርካታ ግዜያት በማገልገል እና ያለፉትን 2 ዓመት ከአዳማ ከተማ ጋር ማሳለፍ የቻለዉን የግራ መስመር ተከላካይ የሆነዉን ደስታ ዩሀንስን በ2 ዓመት ኮንትራት አስፈርሟል።