By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድል አስመዝግቧል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግመቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድል አስመዝግቧል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

ሲዳማ ቡና በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታድየም ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን መቻልን 1 – 0 በማሸነፍ አስመዝግቧል ።

ሲዳማ ቡናዎች በ23ኛው ሳምንት ኢትዮጵያ መድኅንን በረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ ብቻ በማድረግ በሙሉቀን አዲሱ ምትክ አበባየሁ ሀጂሶን ሲያሰልፉ በመቻል በኩል በሳምንቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን በረቱበት ጨዋታ ላይ በነበረው አሰላለፍ ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ጨዋታውን ጀምረዋል ።

የ24ኛው ሳምንታት የመጨረሻ መርሀግብር የነበረው ይህ ጨዋታ ወድድድሩ በሀዋሳ መካሃድ ከጀመረበት ቀን አንስቶ በርካታ ደጋፊዎች ስታድየም ገብተው የተከታተሉት ጨዋታ ሆኗል ።

- ማሰታውቂያ -

በዚህም በበርካታ ደጋፊዎቻቸው ፊት የተጫወቱት እና ውድድሩ ወደ ሀዋሳ ከመጣ በኋላ ተከታታይ ድሎችን ያስመዘገቡት ሲዳማ ቡናዎች በጥሩ መነቃቃት ሆነው ጨዋታውን ጀምረዋል ። በመጀመሪያው አጋማሽም ከተጋጣሚያቸው መቻህ በተሻለ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠሩ ጥረቶችን አድርገዋል ።

በመቻል በኩል ኳስን ከኋላ መስርተው ለመውጣት የሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች እምብዛም ውጤታማ ያልነበሩ ሲሆን ይህ ነው ሊባል የሚችል የግብ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረው ቆይተዋል ።

ወደ መቻል የግብ ክልል ቶለ ቶሎ ሲደርሱ የነበሩት ሲዳማ ቡናዎች በ33ኛው ደቂቃ ላይ መሪ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል ። ሲዳማ ቡና ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች በተመሳሳይ 1 – 0 ሲያሸንፍ የማሸነፊያ ግቦችን ያስቆጠረው ፊሊፕ አጄህ በዚህ ጨዋታም ስሙን በግብ አስቆጣሪነት ላይ አስመዝግቧል ።

ተጫዋቹ ግቡን በግንባር ገጭቶ ኳሱን አመቻችቶ ያቀበለው ደግሞ ይገዙ ቦጋለ ነው ።

ሲዳማ ቡናዎች ከሶሰት ደቂቃዎች በኋላም መሪነታቸውን ከፍ ሊያደርግ የሚችል የግብ ሙከራ በይገዙ ቦጋለ አማካኝነት አድርገው በግብ ጠባቂው ውብሸት ጭላሎ ግብ ከመሆን ድኗል ።

በአጋማሹ መጠናቀቂያ ላይም ሲዳማ ቡናዎች ሌላ ግብ ለማስቆጠር ተቃርበው የነበረ ቢሆንም ምንተስኖት አዳነ ኳሱን ከመስመር ላይ አውጥቶታል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለጊዜ መቻሎች የተሻለ ለመንቀሳቀስ የቻሉበት ነበር ።

የአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ቡድን በአጋማሹ በተጋጣሚው ላይ ብልጫ ወስዶ ለመጫወት ቢችልም ወደ ሲዳማ ቡና የግብ ክልል ደርሰው ጠንካራ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ተቸግረው ቆይተዋል ።

በሲዳማ ቡና በኩል በተወሰደባቸው ብልጫ አብዛኛውን የአጋማሹን ክፍለ ጊዜ በሜዳቸው ላይ ሆነው ለማሳለፍ የተገደዱ ሲሆን በተወሰኑ አጋጣሚዎች በፈጣን መልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴዎች የግብ አጋጣሚዎች ለመፍጠር ሞክረዋል ።

በመጨረሻም ሲዳማ ቡና በአጄህ ግብ 1 – 0 አሸንፏል ።

በ25ኛው ሳምንት ጨዋታዎችም በመጪው ግንቦት 14(ሰኞ) በ9:00 ሲዳማ ቡና ከፋሲል ከነማ ሲጫወት በተከታዩ ቀን ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ መቻል ኢትዮ ኤሌክትሪክን ይገጥማል ።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ እና ሀይቆቹ ጨዋታቸውን በአቻ ውጤት አገባደዋል !!
Next Article ዲኤስቲቪ ቀጣይ 32 ጨዋታዎችን አያስተላልፍም ተባለ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎችThe BiG Interview

የአቶ መኮንን ኩሩ ዝምታን የሠበረ አነጋጋሪ ቃለ-ምልልስ “ውጪ ተምረን መጥተናል፣ ኢንተርናሽናል ላይሰንስ አለን የሚሉ ሰዎች ነገሮች ሁሉ ዓሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል እንዳይሆንባቸው እሰጋለሁ”

Yishak belay By Yishak belay 6 years ago
አለልኝ አዘነ ቅጣት ተላለፈበት
የ2020 የቻን ማጣርያ ጨዋታ ሩዋንዳ ከ ኢትዮጲያ/LIVESCORE/
“ይሄ ቡድን አስቀድሞ ቢኖር ለአፍሪካ ዋንጫ የምናልፍበት ዕድላችን ሙሉ ለሙሉ ይሆን ነበር፤ አሁንም ተስፋ አንቆርጥም” ጌታነህ ከበደ
የኢትዮጵያ ወንድ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የማበረታቻ ሽልማት እና እውቅና ሊበረከትለት ነው ፡፡
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?